(ኢሳት ዲሲ–ታህሳስ 10/2010) አቶ በቀለ ገርባ ለምስክርነት የጠሯቸው የኦሮሚያ ክልል ባላስልጣናት ተለዋጭ ቀጠሮ እንዲሰጣቸው ጠየቁ። ጥያቄውን ያቀረቡት በድርጅታቸው ኦህዴድ በኩል መሆኑ ታውቋል። በሚሰጣቸው ተለዋጭ ቀጠሮም በችሎት ቀርበው ምስክርነት እንደሚሰጡም ለፍርድ ቤቱ በጻፉት ደብዳቤ አስታውቀዋል። ከኦህዴድ ጽሕፈት ቤት ለፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 4ኛ ወንጀል ችሎት ታህሳስ 18/2010 በተጻፈው ደብዳቤ እንደተመለከተው አቶ በቀለ ገርባ በምስክርነት የጠሯቸው የክልሉን ፕሬዝዳንት አቶ ለማ መገርሳን ጨምሮ ...
Read More ».የኢሳት አማርኛ ዜና
ቅዱስ ሲኖዶስ በኢትዮጵያ የተከሰተው የህዝብ ፍጅት እንዲቆም ጥሪ አቀረበ
(ኢሳት ዲሲ–ታህሳስ 19/2010) በስደት የሚገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በኢትዮጵያ የተከሰተው የህዝብ ፍጅት እንዲቆም ጥሪ አቀረበ። መለዮ ለባሽም መሳሪያውን ከሕዝብ ላይ እንዲያነሳ የጠየቀው ቅዱስ ሲኖዶስ የሀገሪቱን ቀውስ ለመፍታት የአደራ መንግስትም እንዲቋቋም ጥሪ አቅርቧል። በብጹዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሪዎስ የሚመራው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ “በሀገር ውስጥና በመላው አለም ለምትገኙ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያን ለምትወዱ ወገኖቻችን” በሚል ርዕስ ጥሪውን አቅርቧል። ሲኖዶሱ ...
Read More »አብያተ ክርስቲያናት ስደተኞችን በማስጠለል ላይ ናቸው
(ኢሳት ዲሲ–ታህሳስ 18/2010) በአሜሪካ የሚገኙ በርካታ አብያተ ክርስቲያናት ስደተኞችን በማስጠለል ላይ መሆናቸው ታወቀ። አብያተክርስቲያናቱ ስደተኞቹን እያስጠለሉ ያሉት የትራምፕ አስተዳደር ሕገወጥ የሚላቸውን ስደተኞች ወደ ሀገራቸው የመመለሱን ስራ በማጠናከሩ ነው። ቢያንስ 32 የሚሆኑ አብያተክርስቲያናት በራቸውን ለስደተኞች ክፍት በማድረግ ስደተኞቹን ከመባረር በመታደግ ላይ ናቸው። የአሜሪካ የስደተኞችና ጉምሩክ ሕግ አስከባሪ መስሪያ ቤት ፖሊሲ በአብያተክርስቲያናት ፣በትምህርት ቤቶች እንዲሁም በሕክምና ተቋማት ፍተሻ ማካሄድን አይፈቅድም። በመሆኑም የመኖሪያ ...
Read More »አቶ ለማ መገርሳና ዶ/ር አብይ አህመድ ፍርድ ቤት ቀርበው ሊመሰክሩ
(ኢሳት ዲሲ–ታህሳስ 18/2010) በእነ ጉርሜሳ አያኖ የክስ መዝገብ በመከላከያ ምስክርነት የተጠቀሱት አቶ ለማ መገርሳና ዶ/ር አብይ አህመድ ፍርድ ቤት ቀርበው ሊመሰክሩ እንደሚችሉ ተገለፀ። ባለስልጣናቱን በአካል አግኝቼ አነጋግሬያቸዋለሁ ያሉት የተከሳሾቹ ጠበቃ አቶ ለማ መገርሳን ጨምሮ ሌሎችም በችሎት ተገኝተው ሊመሰክሩ እንደሚችሉ ገልጸውላቸዋል። በሌላ በኩል የበቀለ ገርባ የመከላከያ ምስክር የሆኑት አቶ አንዱዓለም አራጌ በከባድ ወንጀል የተከሰሱ ናቸው በሚል ማረሚያ ቤቱ ችሎት አላቀርብም ማለቱ ...
Read More »በማህበራዊ ሚዲያዎች ዘመቻ በመካሄድ ላይ
(ኢሳት ዲሲ–ታህሳስ 18/2010) በኢትዮጵያ በግፍ የታሰሩ የህሊናና የፖለቲካ እስረኞችን ለማስታወስ በማህበራዊ ሚዲያዎች ዘመቻ በመካሄድ ላይ መሆኑ ታወቀ። በቲውተርና በፌስቡክ እየተካሄደ ባለው በዚሁ ዘመቻ በመላው ዓለም ኢትዮጵያውያን ተሳታፊ ሆነዋል። በየእስር ቤቱ በስቃይ ላይ የሚገኙትንና በግፍ የተገደሉትን ኢትዮጵያውያን ፎቶግራፎች በመለጠፍና ስቃያቸውን በመዘርዘር ትኩረት እንዲያገኝ መደረጉን ለማወቅ ተችሏል። ዘመቻውን የሚያስተባብሩት በኢትዮጵያ የሚገኙ ጋዜጠኞችና የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ግለሰቦች እንደሆኑም ታውቋል። ዛሬ ፌስቡኩ በኢትዮጵያውያን አንድ ...
Read More »የአማራና የኦሮሞ ተማሪዎች ላይ የተለየ ክትትልና ወከባ እየተፈጸመ ነው
(ኢሳት ዲሲ–ታህሳስ 18/2010) በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ አመጽ ይቀሰቀሳል በሚል ስጋት የአማራና የኦሮሞ ተማሪዎች ላይ የተለየ ክትትልና ወከባ እየተፈጸመ መሆኑ ተገለጸ። በየመኝታ ክፍሉ ደህንነቶች እየገቡ ተማሪዎችን እንደሚያስፈራሩም የደረሰን መረጃ አመልክቷል። ባለፈው ሰኞ ከዩኒቨርስቲው ታፍነው የተወሰዱ ተማሪዎችም የት እንደደረሱ የታወቀ ነገር የለም። ኢሳት ያነጋገራቸው የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች እንደሚሉት ባለፈው ሰኞ ታቅዶ የነበረውና የተወሰኑ ተማሪዎች መታሰራቸውን ተከትሎ በግቢው ውስጥ ብዛት ያለው ሲቪል ...
Read More »የኢህአዴግ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላት ስብሰባ ተቋረጠ
(ኢሳት ዲሲ–ታህሳስ 18/2010) ለሁለት ሳምንት ያህል ሲካሄድ የቆየው የኢህአዴግ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላት ስብሰባ መቋረጡ ተገለጸ። አቶ ገዱ አንዳርጋቸውም አሜሪካ መግባታቸው ታወቋዋል። በሌላ በኩል የኦህዴድና የብአዴን የፓርላማ አባላት ጠቅላይ ሚኒስትሩን ካላነጋገርናቸው በፓርላማ መደበኛ ሰብሰባ ላይ እንደማይገኙ ማሳሰባቸውን ተከትሎ አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ ከሌሎች አመራሮች ጋር በመሆን የፓርላም አባላቱን ማነጋገራቸው ታውቋል። የኦህዴድና የብአዴን የፓርላማ አባላት በህዝበ ላይ እየደረሰ ያለውን በደልና በሐገሪቱ ውስጥ ...
Read More »ሕወሃት ተቃውሞዎችን ለማፈን የማይችልበት ደረጃ ላይ ደርሷል ተባለ
(ኢሳት ዲሲ–ታህሳስ 18/2010) የህወሃት መንግስት በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የሚነሱ ህዝባዊ ተቃውሞዎችን ለማፈን የማይችልበት ደረጃ ላይ መደረሱ ተገለጸ። በኦሮሚያና በአማራ ክልሎች የተነሱትን ተቃውሞዎች ለመቆጣጠር ከድንበር ሰራዊቱን እያንቀሳቀሰ መሆኑም ተገልጿል። የአባይን ግድብ የሚጠብቀው የህዳሴ ዲቪዥን በመባል የሚጠራው የፌደራል ፖሊስ አንድ ሻለቃ ጦር በአማራ ክልል በዩኒቨርስቲዎች የተነሳውን ተቃውሞ ለማስቆም ከግድቡ መንቀሳቀሱም ታውቋል። አገዛዙ የሰራዊት እጥረት በመግጠሙም የትግራይ ሚሊሻዎችና ደህንነቶችን የፌደራል ፖሊስ ዩኒፎርም ...
Read More »የኦሮሚያ ክልል ባለስልጣናትን ተጠያቂ ለማድረግ እንቅስቃሴ ተጀመረ
(ኢሳት ዲሲ–ታህሳስ 18/2010) በኦሮሚያና በኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል የተከሰተውን ግጭት ለማባባስና የኦሮሚያ ክልል ባለስልጣናትን ተጠያቂ ለማድረግ እንቅስቃሴ ተጀመረ። በሕወሃቱ አመራር አቶ ጌታቸው አሰፋ የሚመራው የደህንነት መስሪያ ቤት ይህንን ተግባራዊ ለማድረግ በሰፊው በመንቀሳቀስ ላይ መሆኑንም መረጃዎች አመልክተዋል። ይህንን ለማስፈጸም የፓርቲና የመንግስት መገናኛ ብዙሃን እንዲሁም የመዝናኛ ጣቢያ ጋዜጠኞችን ጭምር የጉዞና የውሎ አበል ከፍሎ ማሰማራቱን መረዳት ተችሏል። የሕወሃት ተቋማት ከሆኑት ኢ ኤን ኤን ቴሌቪዥን ...
Read More »የላይቤሪያ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ በድጋሚ ተካሄደ
(ኢሳት ዲሲ–ታህሳስ 17/2010) የላይቤሪያ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ በድጋሚ ተካሄደ። ባለፈው ጥቅምት በተካሄደው ምርጫ 50 በመቶ ድምጽ ያገኘ ተወዳዳሪ ባለመኖሩ ምርጫው በድጋሚ እንዲካሄድ ተደርጓል። በምርጫው ታዋቂው የእግር ኳስ ተጫዋች ጆርጅ ዊሃና ምክትል ፕሬዝዳንቱ ጆሴ ቦአካይ ዋና ተፎካካሪዎች መሆናቸው ታውቋል። በ19ኛው ክፍለ ዘመን ከአሜሪካ ከባርነት ነጻ በወጡ አፍሪካውያን የተመሰረተችው ላይቤሪያ ላለፉት 73 አመታት ሰላማዊ የስልጣን ሽግግር ተደርጎባት አያውቅም። የአሁኑ ምርጫ ከአንድ በዲሞክራሲያዊ መንገድ ...
Read More »