(ኢሳት ዲሲ–ጥር 14/2010) በሕዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ ውስጥ የተፈጠረው ቀውስ መፍትሄ ባላገኘበት በአሁኑ ወቅት አቶ ስዬ አብርሃ ሀገር ቤት መግባታቸው ታወቀ። በአቶ ስብሃት ነጋ የሚደገፈው የዶክተር ደብረጺዮን ቡድን በአቶ አባይ ወልዱ ቡድን ላይ የጀመረውን ጥቃት በመቀጠልም ወይዘሮ አዜብ መስፍንን ከኤፈርት ሃላፊነት ማንሳቱንም የሕወሃት ደጋፊ የመረጃ ማዕከላት ዘግበዋል። ከአንጋፋዎቹ የሕወሃት ታጋዮች አንዱ የነበሩትና የሕወሃት ጦር አዛዥ በኋላም የመከላከያ ሚኒስትር ሆነው ያገለገሉት ...
Read More ».የኢሳት አማርኛ ዜና
በወልዲያ በአገዛዙ ታጣቂዎች የተፈጸመው ጅምላ ግድያ ተወገዘ
(ኢሳት ዲሲ–ጥር 14/2010) በወልዲያ በጥምቀት በዓል ማግስት በቃና ዘገሊላ በዓል ላይ በአገዛዙ ታጣቂዎች የተፈጸመውን ጅምላ ግድያ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎችና የሲቪክ ማህበራት በጽኑ አወገዙ። ፓርቲዎቹና የሲቪክ ማህበራቱ ግድያውን አስመልክቶ ባወጡት መግለጫ እንዳሉት በሕወሃት/ኢሕአዴግ የሚመራውን አገዛዝ ለማስወገድ ሕዝቡ በጋራ እንዲነሳ ጥሪ አቅርበዋል። በመላው ኢትዮጵያ የሚካሄደው የጸረ ሕወሃት ትግልን ማቀናጀት ቅድሚያ ሊሰጠው የሚገባ ጉዳይ መሆኑንም ገልጸዋል። የአርበኞች ግንቦት ሰባት ለአንድነትና ለዲሞክራሲ ንቅናቄ በአገዛዙ ...
Read More »በወልዲያ ከ7 በላይ ሰዎች የተገደሉት ወጣቶች ባስነሱት ግጭት ምክንያት ነው ተባለ
(ኢሳት ዲሲ–ጥር 14/2010) በወልዲያ በቃና ዘገሊላ በዓል ላይ ከ7 በላይ ሰዎች የተገደሉት የተለየ የፖለቲካ አመለካከት ያላቸው ወጣቶች ባስነሱት ግጭት ምክንያት ነው ሲሉ የሰሜን ወሎ ዞን ፖሊስ መምሪያ ሃላፊ ገለጹ። መምሪያ ሃላፊው ኮማንደር አማረ ጎሹ የአካባቢው ታጣቂዎች ትዕግስታቸው በማለቁ ርምጃውን ለመውሰድ ተገደዋል ብለዋል። ወጣቶቹ ግን በጭፈራ ከመቃወም ውጪ የፈጸሙት ነገር አለመኖሩን የአይን እማኞች ተናግረዋል። የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ...
Read More »በወልዲያ የተቀሰቀሰው ተቃውሞ እንደቀጠለ ነው
(ኢሳት ዲሲ –ጥር 14/2010) በወልዲያ የተቀሰቀሰው ተቃውሞ ለ3ኛ ቀን መቀጠሉ ታወቀ። ትላንት ምሽቱን በከተማዋ የተለያዩ አካባቢዎች ከስርዓቱ ጋር ግንኙነት ያላቸው ግለሰቦች ንብረት ላይ ርምጃ ሲወሰድ እንደነበር የደረሰን መረጃ ያመለክታል። ዛሬ ጠዋት ነዋሪው በዋና ዋና ጎዳናዎች ላይ ተቃውሞ ማድረጉም ተመልክቷል። የአጋዚ ወታደሮችን ተኩሶ የገደለው ወጣት የቀብር ስነስርዓት በተቃውሞ ታጅቦ ተከናውኗል። ዛሬም በአጋዚ ወታደሮች ግድያ መፈጸሙ ታውቋል። ተጨማሪ ሃይል ወደ ከተማዋ ያስገባው ...
Read More »የጥምቀት በዓል ተከበረ
(ኢሳት ዲሲ–ጥር 11/2010) በየዓመቱ ጥር 11 የሚከበርው የጥምቀት በዓል በመላው ዓለም በሚገኙ የክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ በድምቀት ተከበረ። በኢትዮጵያ በበዓሉ አከባበር ላይ ስርዓቱን የሚቃወሙ ድምጾች በብዛት መሰማታቸው ታውቋል። በኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ዘንድ በድምቀት ከሚከበሩ በዓላት መካከል አንደኛው የጥምቀት በዓል ነው። በዘንድሮው የጥምቀት በአልም በርካታ የእምነቱ ተከታዮች በዓሉ በሚከበርባቸው ቦታዎች በመገኘት ሃይማኖታዊ ስነስርዓቱን ተካፍለዋል። በበዓሉ ዋዜማ በሚከበረው የከተራ በዓልም ታቦታቱ ከየደብራቸው ...
Read More »በካሽሚር ግዛት አዲስ ውጥረት ነገሰ
(ኢሳት ዲሲ–ጥር 11/2010) ሕንድና ፓኪስታን በሚወዛገቡባት የካሽሚር ግዛት አዲስ ውጥረት ነገሰ። የህንድ ወታደሮችን ጨምሮ በትንሹ 5 ሰዎች መገደላቸውን ተከትሎ በሁለቱ ሀገራት ወታደሮች መካከል የተኩስ ልውውጥ መካሄዱም ታውቋል። እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር በ2003 የተካሄደውን የተኩስ ማቆም ስምምነትን ተከትሎ ጃሙና ካሽሚር በተባለ ስፍራ ላይ እንዲወሰኑ የተደረገውን ወታደራዊ የድንበር መስመር የተቀበሉ ቢሆንም በቀደሙት አመታት ህንድ ፓኪስታንን ስትወነጅል ቆይታለች። ሆኖም ከ15 አመታት ወዲህ የአሁኑ ከፍተኛና ...
Read More »የሕወሃትን አገዛዝ ለማዳከም የሚያስችሉ አቅጣጫዎችን የሚያሳይ ጥሪ ተላለፈ
(ኢሳት ዲሲ–ጥር 11/2010) ኢትዮጵያውያን የውጭ ምንዛሪ ወደ ሀገር ውስጥ ባለመላክ የሕወሃትን አገዛዝ ለማዳከም የሚያስችሉ አቅጣጫዎችን የሚያሳይ ጥሪ ተላለፈ። አለም አቀፍ የኢትዮጵያውያን የጋራ ግብረ ሃይል ለኢትዮጵያውያን ያስተላለፈው ጥሪ 3 መንገዶችን በመጠቀም የሕወሃትን አገዛዝ ማዳከም እንደሚቻል አመላክቷል። አንደኛው ዌስተርን ዩኒየንና መኒግራምን ከመጠቀም ይልቅ ሌሎች አማራጮችን መጠቀም የሚል ነው። በ2ኛ ደረጃ ደግሞ ሌሎች አማራጮች ካልተገኙና በባንክ በኩል መላክ የግድ ከሆነ የሚላከውን ገንዘብ መጠን ...
Read More »ኢትዮጵያና ሱዳን የጋራ ወታደራዊ ሃይል ለማስፈር ተስማሙ
(ኢሳት ዲሲ–ጥር 11/2010) ኢትዮጵያና ሱዳን የጋራ ወታደራዊ ሃይል በድንበሮቻቸው አካባቢ ለማስፈር ተስማሙ። ሁለቱ ሀገራት የጋራ ወታደሮቻቸውን የሚያሰፍሩት የአባይ ግድብ በሚገኝበት የቤንሻንጉል ክልልና በሱዳን የብሉናይል ግዛት ድንበሮች አቅራቢያ ነው። በሱዳኑ የብሉናይል ግዛት ዋና ከተማ ዳማ ዚን የተፈረመው ስምምነት የተካሄደው በአፍሪካ ቀንድ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየተከሰተ ያለውን ውጥረት ተከትሎ መሆኑ ታውቋል። በአፍሪካ ቀንድ ባሉ ሀገራት ከወትሮው የተለየ ውጥረት መንገሱ ይነገራል። ምክንያቱ ደግሞ ...
Read More »የሳሊተ ምህረት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ውዝግብ እንደቀጠለ ነው
(ኢሳት ዲሲ–ጥር 11/2010) በአዲስ አበባ ሳሊተ ምህረት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን የተፈጠረው ውዝግብ እንደቀጠለ መሆኑ ተሰማ። ትላንት በጥምቀት በዓል ዋዜማ በአካባቢው የተኩስ እሩምታ እንደነበረ የደረሰን መረጃ አመልክቷል። የፌደራል ፖሊስ የቤተክርስቲያኒቱ አገልጋዮችን በጅምላ በማፈስ ካሰረ በኋላ በህዝብ ተቃውሞ መፈታታቸው ታውቋል። የቤተክርስቲያኒቱን ሀብትና ንብረት ከዘረፋ ለመታደግ ህዝቡ የጀመረውን ትግል ለማስቆም በህወሃት አገዛዝና በፓትርያርኩ የሃይል ርምጃ መወሰዱ ውጥረቱን እንዳባባሰው የኢሳት ምንጮች ገልጸዋል። የውዝግቡ መነሻ ...
Read More »ወታደራዊ ምልመላ ተጀመረ
(ኢሳት ዲሲ–ጥር 11/2010) የመከላከያ ሚኒስቴር በመላ ኢትዮጵያ ወታደራዊ ምልመላ ጀመረ። በክልሎችና በአዲስ አበባ ከተማ ጭምር የተጀመረው ወታደራዊ ምልመላ አላማ ምን እንደሆነ ግን አልታወቀም። ይህ በመከላከያ ሰራዊቱ ፕሮግራም በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ጭምር የተሰራጨው ምልመላ እስከ ጥር መጨረሻ እንደሚዘልቅም ከወጣው መርሃ ግብር መረዳት ተችሏል። እድሜያቸው 18 አመትና ከዚያ በላይ የሆኑ ወጣቶች እንዲመዘገቡ ጥሪ የሚያቀርበው የመከላከያ ሚኒስቴር ማስታወቂያ በመላ ሀገሪቱ በየቀበሌ ጽሕፈት ቤቶች ...
Read More »