.የኢሳት አማርኛ ዜና

ሁለት የእርዳታ ሠራተኞች ተገደሉ

(ኢሳት ዲሲ–የካቲት 13/2010) በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ሁለት የዕርዳታ ሠራተኞች ተገደሉ። የፈረንሣይ መንግሥታዊ ያለሆነ ተቋም ሃይድሮሊክ ሣን ፍሮንቴይር ባልደረባ የነበሩት ሀለቱ ግለሠቦች የተገደሉት ባለፈው ቅጻሜ መሆኑ ታውቋል። የገዳዮቹ ማንነት እስካሁን አልታወቀም። በምሥራቃዊ የኮንጎ ኪቩ በተባለው ግዛት የተገደሉት ሁለቱ የዕርዳታ ድርጅት ሰራተኞች በስምና በዜግነት አለመገለፃቸውን ከቢቢሲ ዘገባ መረዳት ተችሏል፡፡ በከፍተኛ የፖለቲካ ውጥረት ውስጥ በምትገኘው ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ በአንድ ዓመት ግዜ ውስጥ የተገደሉት ...

Read More »

እነ ጄኔራል ተፈራ ማሞ አሁንም አልተፈቱም

(ኢሳት ዲሲ–የካቲት 13/2010) ክሳቸው ተቋርጦ እንዲሁም በፕሬዝዳንቱ ይቅርታ ይፈታሉ ከተባሉ የፖለቲካ እስረኞች ውስጥ እነ ጄኔራል ተፈራ ማሞ እንዲሁም የሰማያዊ ፓርቲ አመራር የነበረው ዮናታን ተስፋዬ አሁንም አለመፈታታቸው ታወቀ። በክስ መቋረጥም ሆነ በይቅርታ ስማቸው ያልተጠቀሰው አቶ አንዳርጋቸው ጽጌንና የኢትዮጵያ አየር ሃይል አብራሪ መቶ አለቃ በሃይሉ ገብሬን ጨምሮ ሌሎች የፖለቲካ እስረኞችም እንዲፈቱ ኢትዮጵያውያን በማህበራዊ መድረክ ዘመቻ ጀምረዋል። ከጎንደሩ ሕዝባዊ አመጽ ጋር በተያያዘ ከታሰሩት ...

Read More »

የኢትዮጵያ ሕዝብ ፍላጎት ከአንድ አምባገነን ወደ ሌላ አምባገነን መሸጋገር አይደለም ተባለ

(ኢሳት ዲሲ–የካቲት 13/2010) የኢትዮጵያ ሕዝብ ፍላጎት ከአንድ አምባገነን ወደ ሌላ አምባገነን አገዛዝ መሸጋገር አለመሆኑን የአርበኞች ግንቦት ሰባት ሊቀመንበር ፕሮፈሰር ብርሃኑ ነጋ ገለጹ። ፕሮፈሰር ብርሃኑ ነጋ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ባስተላለፉት የቪዲዮ መልዕክት የምንታገልለት ለውጥ የኢትዮጵያን ሕዝብ ይሁንታ ያገኘ የሽግግር መንግስት እንዲመሰረት ማድረግ ይኖርበታል ብለዋል። በለውጡ ሂደት ስልጣን ሃላፊነት በሌላቸው እጅ እንዳይገባ በከፍተኛ የሃላፊነትና የአጣዳፊነት ሁኔታ መታገል አለብን ሲሉም ገልጸዋል። ፕሮፈሰር ብርሃኑ ...

Read More »

በወልቂጤ የተጠራው አድማ ለሰባተኛ ቀን እንደቀጠለ ነው

(ኢሳት ዜና–የካቲት 13/2010) በጉራጌ ዞን በወልቂጤ ከተማ የተጠራው አድማ ለሰባተኛ ቀን መቀጠሉ ተገለጸ። የገዢው ፓርቲ አባላት የሆኑ ሁለት ሰዎች አድማውን አስተባብራችኋል ተብለው ታስረዋል። በእንድብርና በአገና የፌደራል ፖሊስ የሃይል ርምጃ እየተጠቀመ ነው። የጉራጌ ወጣቶች ጥሪ አድረግዋል። በወልቂጤ የተጀመረው አድማ ሳምንቱን ደፍኗል። ዛሬም ወደ እንቅስቃሴ አልገባችም። ባለፉት ሁለት ቀናት አንዳንድ የንግድ ቦታዎች ተከፍተው የነበረ ቢሆንም ከዛሬ ጠዋት ጀምሮ ሙሉ በሙሉ መዘጋታቸውን የደረሰን ...

Read More »

የስራ ማቆምና በቤት ውስጥ የመቀመጥ አድማው እንደቀጠለ ነው

(ኢሳት ዲሲ–የካቲት 13/2010) በአማራ ክልል የተጠራው የስራ ማቆምና በቤት ውስጥ የመቀመጥ አድማ ለሁለተኛ ቀን መቀጠሉ ታወቀ። በመጀመሪያው ቀን አድማ ያልተሳተፉ ከተሞች ዛሬ ተቀላቅለዋል። ጎንደር በተጠናከረ መልኩ የአድማውን እንቅስቃሴ እያደረገች ነው። በባህርዳር በአብዛኛው ሱቆችና መደብሮች ተዘግተዋል። ባህርዳር ከትላንት ይልቅ ዛሬ አድማ ላይ ጠንክራ ብቅ ብላለች። በአገዛዙ ታጣቂዎች ወከባ ከፍተው የነበሩ አንዳንድ የንግድ ቦታዎች ዛሬ ከረፋድ ጀምሮ አድማውን መቀላቀላቸውን የደረሰን መረጃ አመልክቷል። ...

Read More »

በጉራጌ ዞን የተጀመረው አድማ ለ6ኛ ቀን ቀጥሎአል

በጉራጌ ዞን የተጀመረው አድማ ለ6ኛ ቀን ቀጥሎአል (ኢሳት ዜና የካቲት 13 ቀን 2010 ዓ/ም) በወልቂጤ፣ በጉብሬ፣ በአገናና በሌሎችም አካባቢዎች የተጀመረው የስራ ማቆም አድማና ተቃውሞ ለስድሰተኛ ቀን መቀጠሉን ከስፍራው የደረሰን መረጃ ያመለክታል። የስራ ማቆም አድማው ወደ አደባባይ ተቃውሞ ተሸጋግሮ የተወሰኑ ሰዎች በጸጥታ ሃይሎች መገደላቸው ይታወሳል። ተቃውሞው አድማሱን በማስፋት ወደ እዣ፣ ቺሃ፣ እምድብር፣ እነሞር እና ኢነር ወረዳ የጉመር ወረዳን መቀላቀላቸውን ወኪላችን ገልጿል። ...

Read More »

በጎንደርና ባህርዳር የስራ ማቆም አድማው ለሁለተኛ ቀን ቀጥሏል

በጎንደርና ባህርዳር የስራ ማቆም አድማው ለሁለተኛ ቀን ቀጥሏል (ኢሳት ዜና የካቲት 13 ቀን 2010 ዓ/ም) በአማራ ክልል የተጠራው የስራ ማቆም አድማ በጎንደር ከተማ ለሁለተኛ ቀን በተጠናከረ ሁኔታ ቀጥሎአል። በከተማው ምንም አይነት የንግድ እንቅስቃሴውም ሆነ የተሽከርካሪ አገልገሎት የለም። የአገዛዙ ካድሬዎች የንግድ ድርጅቶችን ለማስከፈት ያደረጉት ጥረት እንዳልተሳካ ከስፍራው የደረሰን መረጃ ያመለክልታል። በባህርዳር ትናንት የተጀመረውን አድማ ተከትሎ የአገዛዙ ባለስልጣናትና ሰራተኞች የንግድ ድርጅት ባለቤቶችን ...

Read More »

ወጣት ንግስት ይርጋን ጨምሮ የተወሰኑ እስረኞች ክሳቸው ተቋርጦ ተፈቱ

ወጣት ንግስት ይርጋን ጨምሮ የተወሰኑ እስረኞች ክሳቸው ተቋርጦ ተፈቱ (ኢሳት ዜና የካቲት 13 ቀን 2010 ዓ/ም) በሰሜን ጎንደር ተጀምሮ በአማራ ክልል የተቀጣጠለውን ህዝባዊ ተቃውሞ ፊት ሆነው ከመሩትና ካስተባበሩት መካከል በግንባር ቀደምነት የምትጠራዋ ወ/ት ንግስት ይርጋ ከሷ ተቋርጦ ከእስር ቤት ወጥታለች። በሽብር ወንጀል የተከሰሰችው ወ/ት ንግስት ከጎንደር ወደ አዲስ አበባ ማእከላዊ እስር ቤት በተዘዋወረችበት ወቅት ከፍተኛ የሆነ ሰብአዊ መብት ጥሰት ተፈጽሞባታል።ወ/ት ...

Read More »

እንግሊዝ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መታወጁ እንደሳዘናት ገለጸች

እንግሊዝ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መታወጁ እንደሳዘናት ገለጸች (ኢሳት ዜና የካቲት 13 ቀን 2010 ዓ/ም) የአገሪቱ የውጭ ግንኙነት መስሪያ ቤት ባወጣው መግለጫ፣ “ ወዳጃችን እና አጋራችን ኢትዮጵያ አሳሳቢ በሆነ ጊዜ ላይ ትገኛለች” ብሎአል። ስርዓት ባለው መልኩ የፖለቲካ ለውጥ ለማምጣት የሚደረገው ጥረት አወንታዊ ቢሆንም፣ ይህንን ጥረት የሚያበላሽ ፣ አሳሳቢና አሳዛኝ የሆነ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ታውጇል ሲል በአዋጁ ላይ ያለውን ተቃውሞ ገልጽ አድርጓል። ...

Read More »

በአማራ ክልል የተለያዩ ከተሞች የስራ ማቆም አድማ ተጀመረ

በአማራ ክልል የተለያዩ ከተሞች የስራ ማቆም አድማ ተጀመረ (ኢሳት ዜና የካቲት 12 ቀን 2010ዓ/ም) በጎንደር፣ በደብረታቦርና በባህርዳር ከተሞች ሰኞ የካቲት 12 ቀን 2010 ዓ.ም የስራ ማቆም አድማ ተጀምሯል። በጎንደር በመካሄድ ላይ ባለው አድማ የትራንስፖርት አገልግሎት ሙሉ በሙሉ ተቋርጧል። የንግድ ድርጅቶችም እንዲሁ ተዘግተዋል። ወጣቶች በተለያዩ አደባባዮች ተሰባስበው በመታዬት የንግድ ድርጅቶችን ለማስከፈት የሚያስገድዱትን ባለስልጣናት ሲያስጠነቅቁ ታይተዋል። በሁሉም የከተማዋ አካባቢዎች የስራ ማቆም አድማው ...

Read More »