የጋዜጠኛ ግሩም ተክለሐይማኖት ደህንነት አደጋ ላይ ነው ተባለ

መስከረም ፲ (አስር) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም

ኢሳት ዜና:-የአስኳልና ሳተናው ዋና አዘጋጅ የነበረው በየመን አገር በስደት ላይ የሚገኘው ጋዜጠኛ ግሩም ተክለሐማኖት  በየመን ፖሊሶች እየተዋከ ነው።

ጋዜጠኛው ጳጉሜ 3 ቀን 2004 ዓም ቤቱ በሌሊት በፖሊስ እንደተፈተሸበት ለኢሳት ተናግሯል::    ጋዜጠኛ ግሩም ችግሩን ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስደተኞች ኮሚሽን ቢያመለክትም ጽሁፍ መጻፉን እንዲያቆምና ቤት እንዲቀይር ከመጠየቅ ውጭ ችግሩን የሚያቃልል መልስ ሊሰጠው አልቻለም፡።

ጋዜጠኛ ግሩም ኢትዮጵያውያን ተረባርበው ከችግሩ እንዲታደጉት ጥሪ አቅርቧል::

በመጨረሻም ኢሳት በአጭር ሞገድ ለሚተላለፈው ዝግጅቱ  የፍሪኮንሲ ለውጥ ያደረገ ሲሆን አዲሱ ፍሪኮንሲም 15360 ኪሎ ህርዝ መሆኑን ለመግለጥ እንወዳለን።

___________________________________________________________________________________________________________________________________________________________________________

ESAT is the first independent Ethiopian satellite service tasked to produce accurate and balanced news and information, as well as other entertainment, sports and cultural programming created for and by Ethiopians.

ESAT is committed to the highest standards of broadcast journalism and programming and will strive to provide an outlet of expression to all segments of the diverse Ethiopian community worldwide