የአማራ ተወላጆች ከቤንች ማጂ ዞን እንዲወጡ ማዘዛቸው ኢህአዴግ ደቡቡንና አማራውን ለማጋጨት የቀየሰው ሴራ ነው ተባለ

 

ሚያዚያ ፬ (አራት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም

ኢሳት ዜና:-አቶ ሽፈራው ሽጉጤ የአማራ ተወላጆች ከቤንች ማጂ ዞን እንዲወጡ ማዘዛቸው ኢህአዴግ ደቡቡንና አማራውን ለማጋጨት የቀየሰው ሴራ ነው ሲሉ የአንድነት ፓርቲ የደቡብ ተወካይ ገለጡ

የአንድነት ፓርቲ የምክር ቤት አባልና የደቡብ ተወካይ የሆኑት አቶ ዳንኤል ሺበሺ ለኢሳት እንደተናገሩት በአቶ ሽፈራው ሽጉጤ የተጻፈው መመሪያ አንድን ብሄር ነጥሎ ለማጥቃት ያለመ ነው

ኢህአዴግ ከዚህ ቀደም ሲያደርግ እንደነበረው ሁሉ የአሁኑ እርምጃውም ደቡቡን ከአማራው ህዝብ ጋር ለማጋጨት የቀየሰው ሴራ ነው። የዚህ ሁሉ ችግር መነሻው ኢህአዴግ የሚከተለው የብሄር ፖለቲካ መሆኑን አቶ ዳንኤል አስምረውበታል ።

ሰፋሪዎች ስርአቱን ተከትለው አልሰፈሩም ከተባለ ለምን አስቀድሞ ለመከላከል አልተሞከረም ሲሉ የሚጠይቁት አቶ ዳንኤል ፣ ሰዎች ቋሚ ንብረት ካፈሩና ቤተሰብ ከመሰረቱ በሁዋላ እየተደበደቡ ከክልሉ እንዲወጡ የተደረገው አሰራር አሳዛኝ ነው

በቅርቡ የደቡብ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ሽፈራው ሽጉጤ ከክልሉ የተባረሩት ሰዎች በቁጥር 800 የአማራ ተወላጆች ብቻ ናቸው በማለት ለሰጡት አስተያየት ደግሞ አቶ ዳንኤል የሚከተለውን ብለዋል

በክልሉ ከማዳበሪያ እዳ እና ከፍትህ እጦት ጋር በተያያዘ በርካታ ሰዎች ራሳቸውን እያጠፉ ነው እየተባለ ነው፣ ይህንንስ ድርጅታችሁ ያውቃል ወይ ተብለው የተጠየቁት አቶ ዳንኤል ፣ ማዳበሪያ በክልሉ ትልቅ አደጋ እያመጣ መሆኑን ገልጠዋል

በዳውሮ ዞን አቶ አባተ አየለ የተባሉት  ሰው ፍትህ ካልተሰጠኝ ራሳቸውን ከዛፍ ላይ ፈጥፍጠው እንደሚገድሉ በመዛታቸው ከመንግስት ባለስልጣናት በተደረገላቸው ድለላ ከዛፍ ላይ እንዲወርዱ መደረጉን መዘገባችን ይታወሳል።

________________________________________________________________________________________

ESAT is the first independent Ethiopian satellite service tasked to produce accurate and balanced news and information, as well as other entertainment, sports and cultural programming created for and by Ethiopians.

ESAT is committed to the highest standards of broadcast journalism and programming and will strive to provide an outlet of expression to all segments of the diverse Ethiopian community worldwide