የሱዳን የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች የተቃውሞ ሰልፍ እያደረጉ ነው።

ሰኔ አስራ ሦስት ቀን ፳፻፬ ዓ/ም

ኢሳት ዜና:-ተማሪዎቹ ተቃውሞውን ያነሱት መንግስት በአገሪቱ የሚታየውን የዋጋ ንረት ለመቆጣጠር የሚወስደውን እርምጃ ተከትሎ ነው።

የአገሪቱ ተቃዋሚዎች ህዝቡ በፕሬዚዳንት አልበሽር መንግስት ላይ እንዲነሳ ጥሪ እያቀረቡ ነው።

የበሽር መንግስት በተማሪዎች ላይ የሚወስደውን እርምጃ የአሜሪካ መንግስት አውግዟል።

አመጹ በካርቱም ብቻ ሳይሆን ከካርቱም ውጭ ባሉ ዋና ዋና ከተሞችም ተሸጋግሯል።

ተቃውሞውን ለመዘገብ ወደ ዩኒቨርስቲዎች የተጓዙ የውጭ አገር ጋዜጠኞችም በጸጥታ ሀይሎች ተይዘዋል።

ESAT is the first independent Ethiopian satellite service tasked to produce accurate and balanced news and information, as well as other entertainment, sports and cultural programming created for and by Ethiopians.

ESAT is committed to the highest standards of broadcast journalism and programming and will strive to provide an outlet of expression to all segments of the diverse Ethiopian community worldwide