የሱማሌ ክልል ፕሬዚዳንት በዋሽንግተን ዲሲ  ለደረሰባቸው የኢትዮጰያውያን ተቃውሞ የብልግና ምላሽ ሰጡ።

መጋቢት ፪(ሁለት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የሱማሌ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ አብዲ መሀመድ ኡመር በዋሽንግተን ዲሲ ከፍተኛ ተቃውሞ አጋጠማቸው።

ፕሬዚዳንቱ በተገኙበት ሆቴል የተገኙ ኢትዮጰያውያን ፦” ሰውዬው እጃቸው በደም የተጨማለቀ፣ የሱማሌ ክልል ወጣቶችን በመግደል በዘር ማጥፋት ክስ የተመሰረተባቸውና  እና ለዚህም  በዓለማቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት ሊጠየቁ የሚገባ  ወንጀለኛ መሆናቸውን በማውሳት ከፍ ያለ ተቃውሞ አሰምተዋል።

በደረሰባቸው ድንገተኛ ተቃውሞ  የተበሳጩ የመሰሉት የክልሉ ፕሬዚዳንት አቶ አብዲ መሀመድ  በተደጋጋሚ ጸያፍ ቃል ሲናገሩ ተደምጠዋል። ስለ ሁኔታው መረጃ ደርሰሠቸው በስፍራው የደረሱ የሴኩሪቲ ሰራተኞችም   ተቃውሞውን አብረደውታል።