ኬንያ ከአለማቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት አባልነት ለመልቀቅ ወሰነች

ነሃሴ ፴(ሠላሳ)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኬንያ ከአምስት አመታት በፊት የተደረገውን ምርጫ ተከትሎ በሞቱ ከ1ሺ በላይ ዜጎች የአሁኑ አገሪቱ መሪ ኡሁሩ ኬንያታና ምክትላቸው ዊሊያም ሩቶ በሰው ልጆች ላይ በተፈጸመ ወንጀል በአለማቀፉ ፍርድ ቤት ተጠያቂዎች ሆነዋል።

ሁለቱም መሪዎች ፍርድ ቤት እንደሚቀርቡ በሚታወቅበት ሰአት አገራቸውን ከፍርድ ቤቱ አባልነት በማስወጣት ራሳቸውን ከጠጠያቂነት ለማዳን የወሰዱት እርምጃ የአገሪቱን ተቃዋሚዎች አስቆጥቷል።

ሁለቱ መሪዎች ከፍርድ ቤቱ ጋር የማይተባበሩ ከሆነ ፍርድ ቤቱ የእስር ማዘዣ እንደሚያወጣ    አስታውቋል።