ኢትዮጵያውያን በጄኔቭ የተቃውሞ ሰልፍ አደረጉ

መጋቢት ፲፪ (አስራ ሁለት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም 

ኢሳት ዜና:-ኢትዮጵያውያኑ ትናንት ባደረጉት የተቃውሞ ሰልፍ ገዢው ፓርቲ በሙስሊም ኢትዮጵያውያን ጥያቄ ዙሪያ የየዘውን አቋም ከማውገዝ ባለፈ፣ በአገረቱ ውስጥ የሰብአዊ መብቶች ጥሰት እየተባባሰ መምጣቱን ለተባበሩት መንግስታት ድርጅቶች የተለያዩ ክፍሎች አስታውቀዋል።

የሰላማዊ ሰልፉ አስተባባሪ ፣ የቢላል ኮሚቴ መስራችና ዋና ጸሀፊ የሆኑት አቶ ኤልያስ ረሺድ ከኢሳት ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ አንደገለጡት ሰላማዊ ሰልፉ  ሙስሊም ኢትዮጵያን የሚያደርጉትን  ትግል ለአለማቀፉ ማህበረሰብ የማሳወቅ አላማ ነበረው

አቶ ኤልያስ ጉዳያቸውን ለተለያዩ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ክፍሎች ማሳወቃቸውንም ገልጸው፣ ድርጅቶቹ ጉዳዩን በሂደት እንደሚመረምሩ እንደነገሩዋቸውም አብራርተዋል