ኢህአዴግ በሶስት ድርጅቶች ላይ አዲስ ዘጋቢ ፊልም እያዘጋጀ መሆኑ ተሰማ

ታህሳስ ፳፪( ሃያ ሁለት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በመሰራት ላይ ያለው አዲስ ፊልም ኦነግ ፤ ኦብነግ እና ግንቦት ሰባትን በሽብርተኝነት የሚያወግዝ ነው።

ኢህአዴግ በዚህ ሰአት ፊልሙን ለምን ለመስራት እንደፈለገ ግልጽ የሆነ ነገር የለም። አንዳንዶች እንደሚገምቱት ከሆነ ግን ገዢው ፓርቲ በድርጅቶች እንቅስቃሴ ስጋት እየገባው ነው።

እየተሰራ ባለው ፊልም ውስጥ ኢሳትንም ለመወንጀል እየታሰበ መሆኑን ምንጮች አስታውቀዋል። ዘጋቢ ፊልሙ እስካሁን ባለመጠናቀቁ እና የመጨረሻውን የአርትኦት ይለፍ ባለማግኘቱ በይዘቱ ላይ ሙሉ አስተያየት ለመስጠት አላስቻለም።

ኢህአዴግ ሶስቱን ድርጅቶች አሸባሪ ብሎ ከሰየማቸው ጀምሮ ተከታታይ ዘጋቢ ፊልሞችን ሲሰራ ቆይቷል።