አቶ ስብሃት ነጋ ከኢሳት ጋር ቃለ ምልልስ አደረጉ

ጠ/ሚ መለስ ዜናዊ በ10 ቀናት ውስጥ ወደ ስራ ገበታቸው እንደሚመለሱ ከሶስት ሳምንታት በፊት  ስህተት እንደነበር አቶ ስብሃት ነጋ ከኢሳት ጋር ባደርጉት ቃለ  ምልልስ ገለጹ::
አቶ በረከት ስምኦን ከአዲሱ ዓመት በፊት አቶ መለስ ወደስራ ገበታቸው እንደሚመለሱ የሰጡትን መግለጫ በተመለከተ ይህንን የሚያረጋግጥም ሆነ የሚአስተባብል መረጃ እንደሌላቸው አመልክተዋል።
አንጋፋው ሕወሀት ታጋይ አቶ ስብሀት ነጋ ለስርአቱ ቅርበት ያላቸው ጋዜጦች ጠ/ሚ/ር መለስ ዜናዊ ወደ ሀገር ቤት ስለመመለሳቸው በጻፉት ላይ ትያቄ አንስተዋል።
ከሰኔ 11/2004 ጀምሮ ላለፉት 57 ቀናት ጠ/ሚ/ር መለስ ዜናዊን አለማግኘታቸውን አቶ ስብሀት ለኢሳት በሰጡት ቃለምልልስ አመልክተዋል።
የሐገሪቱ ጦር ሀይል አዛዥነቱን ስፍራ የያዘው ማነው? የሚለውን ጨምሮ ጠ/ሚ/ሩ በሕይወት ካሉ ድምጻቸውን ለምን አያሰሙም የሚለውን ጨምሮ ለአቶ ስብሀት ኢሳት ላነሳው ጥያቄ የሰጡትን ምላሽ በድረ-ገጻችን ላይ ይመልከቱ።