በእስር ላይ የሚገኙት የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ጉዳይ በድጋሜ ተቀጠረ

መጋቢት ፱ (ዘጠኝ) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- አለማቀፍ የሴቶችን ቀን ምክንያት በማድረግ በተዘጋጀ ሩጫ ላይ ተቃውሞ አሰምታችሁዋል በሚል ከአስር በላይ ቀናትን በእስር ያሳለፉት የሰማያዊ ፓርቲ 7 ሴት እና 3 ወንድ አመራሮች መጋቢት 5 ቀን 2006 ዓም ጉዳያቸው ለመጨረሻ ጊዜ እንደሚታይና ለዛሬ መጋቢት 9 ውሳኔ እንደሚሰጣቸው በዳኛው ተገልጾ የነበረ ቢሆንም፣ ፖሊስ ጉዳዩ በመደበኛ ፍርድ ቤት እንዲታይ በመጠየቁ ፍርድ ቤቱ ለነገ ቀጠሮ ሰጥቷል።

ፖሊስ ከዚህ ቀደም ምርመራውን በ5 ቀናት አጠናቆ ክስ እንዲመሰርት ቢታዘዘም ፣ ዛሬ የሚያዙ ተጨማሪ 20 ሰዎች አሉ በሚል ተጨማሪ የ14 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ጠይቋል።ጠበቃ አለሙ ጎቤቦ ግን የፖሊስን ጥያቄ አጥብቀው ተቃውመዋል።

ወጣቶቼ የፓርቲው የአመራር አባላት በእስር ቤት ውስጥ መብታቸው እየተጣሰ መሆኑን ገልጸዋል።