በኢትዮጵያ 34 ድርጅቶች ጤፍ ወደ ውጭ በመላክ ላይ ናቸው

ሰኔ ፲፩(አስራ አንድ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከመንግስት የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው የመንግስቱን የእርሻ ሰብል ድርጅት ጨምሮ 34 የንግድ ድርጅቶች ጤፍ ወደ ውጭ አገር በመላክ ላይ ናቸው።

መንግስት በአገሪቱ የጤፍ ምርት እጥረት ማጋጠሙን ተከትሎ ጤፍ ወደ ውጭ እንዳይወጣ አግዶ የነበረ ሲሆን እገዳውን ከ ግንቦት ወር 2005 ጀምሮ  አንስቷል።

አንድ ኩንታል ጤፍ በአዲስ አበባ ከ1800 እስከ 2000 ብር በመሸጥ ላይ ይገኛል።