በኢትዮጵያ የሰብአዊ መብት አያያዝ ዙሪያ የአሜሪካ ኮንግረስ የውይይት መድረክ አዘጋጀ

ኀዳር (አራት) ቀን ፳፻፯ / ኢሳት ዜና :- አለማቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያውያን መብቶች የተባለው ድርጅት ለኢሳት በላከው መግለጫ የቶም ላንሶቶስ የሰብአዊ መብት ኮሚሽን በኢትዮጵያ የሰብአዊ መብቶች አያያዝ ዙሪያ ታዋቂ ሰዎች ሃሳባቸውን እንዲያካፍሉ ጋብዟል።

ተናጋሪዎቹ በኢትዮጵያ ያለውን የሰብአዊ መብት አያያዝ በመገምገም የአሜሪካ መንግስት የዲፕሎማቲክና የገንዘብ ድጋፉን ተጠቅሞ በኢትዮጵያ የሚታየው የተበላሸ የሰብአዊ መብት አያያዝ እንዲሻሻል ግፊት ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል ሲል መግለጫው አመልክቷል።

ዝግጀቱ አርብ ኖቬምበር 14፣ 2014 ከሰአት 1፡ 30 ፒኤም ላይ ይካሄዳል።