በአዋሳ ከተማ ያለው ውጥረት እንደቀጠለ ነው

ሰኔ ፲፮ (አስራ ስድስት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም

ኢሳት ዜና:-የአዋሳ ከተማን እጣ ፋንታ እና የሲዳማ ዞንን የክልል ጥያቄ ተከትሎ በሲዳማ ዞን ተወላጅ የምክር ቤት አባላት በአንድ ጎን እና የፌደራሉና የሌሎች የምክር ቤት አባላት በሌላ ጎን ሆነው  የጀመሩት ውዝግብ እየተካረረ መምጣቱን ተከትሎ በአዋሳ የሚታየው ከፍተኛ ውጥረት አለመቀነሱን ዘጋቢያችን ገልጧል።

በዛሬው እለት ወጣቶች ሰላማዊ ሰልፍ ያደርጋሉ በሚል ስጋት የፌደራል ልዩ ሀይል አድማ በታኝ ፖሊሶች በከተማዋ በጂፕ መኪኖች ላይ ከቦታ ቦታ እየተዘዋወሩ ቅኝት ሲካሂዱ ውለዋል። ዛሬ ምንም አይነት ግጭት አለመከሰቱን የገለጠው ዘጋቢአችን ይሁን እንጅ ውጥረቱ እየጨመረ መምጣቱን ተከትሎ በማንኛውም ሰአት ተቃውሞ ሊነሳ ይችላል በማለት ስጋቱን ገልጧል። ወረቀቶች መበተናቸውን መቀጠላቸውን፣ ሌሊቱን የተኩስ ድምጽ ይሰማ እንደነበር፣ በከተማዋ ዳርቻ የሚገኙ ሱቆች አሁንም ዝርፊያ በመፍራት መዘጋታቸውን ገልጧል።

ጉዳዩን በማስመልከት የአንድነት ፓርቲ ከፍተኛ አመራርና የደቡብ ተወካይ የሆኑትን አቶ ዳንኤል ሽበሽ ለኢሳት እንደተናገሩት፣ በአዋሳ የተነሳው ግጭት ከመልካም አስተዳዳርና ፍትህ እጦት ጋር የተቆራኘ ነው።

በ1994 ዓም በተፈጠረው ችግር በርካታ ዜጎች ማለቃቸውን ያስታወሱት አቶ ዳንኤል፣ የአሁኑ ችግር ከ10 አመት በሁዋላ አገርሽቶ የመጣው መንግስት ችግሩን በወቅቱ ለመመለስ ባለመቻሉ ነው

አሁን በአካባቢው የሚታየው ውጥረት ወደ ብሄረሰብ ግጭት ሊያመራ ይችላል የሚሉ ስጋቶች አሉ፣ እርስዎ እንዴት ያዩታል ለተባሉት አቶ ዳንኤል ስጋቶች መኖራቸውን ተናግረዋል::

___________________________________________________________________________________________________________________________________________________

ESAT is the first independent Ethiopian satellite service tasked to produce accurate and balanced news and information, as well as other entertainment, sports and cultural programming created for and by Ethiopians.

ESAT is committed to the highest standards of broadcast journalism and programming and will strive to provide an outlet of expression to all segments of the diverse Ethiopian community worldwide