በአንዋር መስኪድ ቦንብ ፈንድቶ ሰዎች ቆሰሉ

ታኀሳስ ፩ (አንድ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በታላቁ አንዋር መስጊድ የሶላት ጸሎት በማድረስ ላይ በነበሩ ሙስሊም ዜጎች ላይ በደረሰ ጥቃት ቁጥራቸው በውል ያልተወቀ ሰዎች ተጎድተው ወደ ተክለሃይማኖት ሆስፒታል ተወስደዋል። አደጋውን ማን እንዳደረሰው የታወቀ ነገር የለም።ፖሊሶች በአካባቢው ተገኝተው ሲያጸዱ መታየታቸውን የአይን እማኞች ገልጸዋል።