በሶማሊያ በቦምብ ፍንዳታ 2 የኢትዮጵያ ወታደሮች ተገደሉ

       

ሚያዚያ ፲፮ (አስራ ስድስት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም

ኢሳት ዜና:-በሶማሊያ በቦምብ ፍንዳታ 2 የኢትዮጵያ ወታደሮች ተገደሉ፤በአፀፋዉ ሰላማዊ ዜጎችን ገደሉ        

በሶማሊያ በለደ-ወይኒ ከተማ በመንገድ ዳር በተጠመደ ቦምብ ሁለት የኢትዮጵያ ወታደሮች ሲገደሉ በሰባት ሰዎች ላይ ጉዳት መድረሱን በስፍራዉ የነበሩ የዓይን ምስክሮች መግለፃቸዉን ሬዲዮ ጋራዌ የመረጃ ምንጭ አስታዉቋል።

በዚህም ምክንያት የኢትዮጵያ ወታደሮች በወሰዱት እርምጃ 3 በአካባቢዉ የነበሩ ሰላማዊ ሰዎችን መግደላቸዉና ከሟቾቹ መካከል ሶስተኛዉ ህይወቱን ለማትረፍ የሸሸዉ ሰዉ በወታደሮቹ ማሳደድ የተገደለዉ መኖሪያ ቤቱ አካባቢ እንደደረሰ መሆኑ ታዉቋል።

ከዚሁ ፍንዳታ ጋር በተያያዘ ባላዱል-አሚን ተብሎ በሚጠራዉ የአካባቢዉ መንደር ዉስጥ ነዋሪ የሆኑ 2 ሌሎች ሰዎችን ከመኖሪያ ቤታቸዉ በማዉጣት የኢትዮጵያ ወታደሮች መግደላቸዉን አንድ ስማቸዉ እንዳይጠቀስ የፈለጉ የአይን ምስክር መግለፃቸዉን የዜና ምንጩ በተጨማሪ አስታዉቋል።

ባለፈዉ አመት የኢትዮጵያ ወታደሮች በለደ-ወይኒን ከአልሼባብ አማፅያን ካስለቀቁ ወዲህ በአካባቢዉ የሰብኣዊ መብት ረገጣና ህገወጥ/የጅምላ ግድያ መፈፀማቸዉን በመጥቀስ አለምአቀፉ የሰብኣዊ መብት ተሟጋች ድርጅት ሂዩማን ራይትስ ዎች መክሰሱ ይታወቃል።  

የአልሸባብ የጥቃት እንቅስቃሴ መቀነሱ ሲታወቅ የኢትዮጵያ ጦር ሶማሊያን ለቆ እንደሚወጣ ጠ/ሚር መለስ ዜናዊ መግለፃቸዉን የዜና ምንጩ አመልክቷል።

___________________________________________________________________________________________________________________________________________________

ESAT is the first independent Ethiopian satellite service tasked to produce accurate and balanced news and information, as well as other entertainment, sports and cultural programming created for and by Ethiopians.

ESAT is committed to the highest standards of broadcast journalism and programming and will strive to provide an outlet of expression to all segments of the diverse Ethiopian community worldwide