በሮመዳን ጾም ጅማሮ ሙስሊም ኢትዮጵያውያን ጠንካራ ተቃውሞ አሰሙ

 

ሐምሌ ፭( አምት )ቀን ፳፻፭ ዓ/ም

ኢሳት ዜና :-በአዲስ አበባ በአንዋር መስጊድ ከፍተኛ ህዝብ በተገኘበት ተቃውሞ ተካሂዷል። መንግስት የለም ወይ፣ የሼክ ኑር ኢማም ግድያ ድራማ ነው፣ ድራማው ይብቃ፣      መሪዎቻችን ይፈቱ፣ መሀይም አይመራንም፣ በፍትህ እጦት ድፍን አንድ አመት መንግስት ራሱ ገዳይ ራሱ ከሳሽ፣ ።
አሸባሪው  መንግስት ነው፣  ፍትሕ ማዳን።
ፍትህ እያሉ ቃሊቲ ገቡ ገደሉት ብለው ድራማ ሰሩ።
የመንግስት ወንጀለኞች ለፍርድይቅረቡ።
አሸባሪአይደለንም።
ኢቲቪ ውሸታም ሌባ።
የገደለው መንግሥት ነው።
ኮሚቴው ይፈታ።
አቡኪ አምባሳደር።
ካሚል ሸምሱ አምባሳደር ።
በድሩ ሁሴን አምባሳደር ።
ለዲናችን እንሞታለን።የሚሉና ሌሎችም ተቃውሞዎች ለ45 ደቂቃዎች ያክል ተስተጋብተዋል።

ኢሳት ያነጋገራቸው ሙስሊሞች እንደገለጹት በአንዋር መስጊድ የተካሄደው ተቃውሞ እስከዛሬ ከታዩት ሁሉ የሚልቅ ነው።

በተመሳሳይ ዜናም በወልድያ ከተማ የሚገኙ ሙስሊሞች ‘ መንግስት ድምጻችን ይስማ፣  በመሀይሞች መመራት በቃን፣ መድረሳችን ይመለስ” የሚሉ መፈክሮችን በማሰማት ተቃውሞአቸውን ሲያሰሙ ውለዋል።  በናዝሬት/አዳማ፣ በአሰሳ እና ሻሸመኔም ተመሳሳይ ተቃውሞች ተካሂደዋል።

መንግስት በደሴ በሼክ ኑር ኢማም ግድያ ላይ የሰጠው ትኩረት ብዙ ሙስሊሞችን ማበሳጨቱንና ለዛሬው ከፍተኛ ተቃውሞ መንስኤ መሆኑን ጉዳዩን በቅርብ የታዘቡ ወገኖች ይገልጻሉ።