በህወሃት ውስጥ የተፈጠረውን ክፍፍል በሽምግልና ለመፍታት ጥረት ተጀመረ

ኢሳት (ሚያዚያ 16 ፥ 2009)

በህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ (ህወሃት) ውስጥ የተፈጠረውን ክፍፍል በሽምግልና ለመፍታት የሃገር ሽማግሌዎች እንቅስቃሴ ጀመሩ።

በፕሮፌሰር ኤፍሬም ይስሃቅና በአትሌት ሃይሌ ገ/ስላሴ የተጀመረው ይህ ጥረት የአርበኞች ማህበር ሊቀመንበር/ ልጅ ዳንዔል ጆቴንም እንዳካተተ መረዳት ተችሏል።

በህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ (ህወሃት) አመራር ውስት ረጅም ጊዜያት የዘለቀና ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ገያድ እየወጣ የሚመጣውን ልዩነት ለመሰምገል ከራሱ ከህወሃት የተውጣቱ ገለልተኛ ቡድኖች ያደረጉት ጥረት አልተሳካም። ሆኖም ችግሩ ከህወሃት አጥር ወጥቶ በአደባባይ ምልክት እያሳየ መገኘቱን ተከትሎ እና ፕ/ር ኤፍሬም የሽምግልና ጥረቱን ጀምረዋል። ይህም ጥረት ከቀድሞዎቹ የሽማግሌ ቡድን አባላት ከ እነ አትሌት ሃይሌ ገብረ ስላሴ በተጨማሪ የአርበኞቹ ማህበር ሊቀመንበር የሆኑትን ልጅ ዳንዔል ጆቴን እንዲሁም ነጋዲውዎችን እንደጨመረ መረዳት ተችሏል።

በህወሃት ውስጥ የተፈጠረውን ክልልፍ በተመለከተ ያለው የሃይል አሰላለፍ አንዳንድ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት አንደኛው ወገን በጄኔራል ሳሞራ የኑስ የሚመራ ሲሆን፣ የወታደራዊ መረጃ ሃላፊው ሜ/ጀኔራል ዲላን ጨምሮ እንዲሁም የሜቴክ ስራ አስኪያጅ ሜ/ጄኔራል ክንፈ ዳኘው የዚህ ቡድን ዋና ተዋናዮች መሆናቸው የተገለጸ ሲሆን፣ ወታደሩ በዚሁ ቡድን ስር እንደሆነ ተመልክቷል።

ከፖለቲከኞቹ ውስጥ የዚህ ቡድን አባላትና ተዋናዮቹ የትግራይ ክልል ፕሬዚደንት አቶ አባይ ወልዱ እንዲሁም የቀድሞው ጠ/ሚ/ር መለስ ዜናዊ ባለበት ወ/ሮ አዜብ መስፍን ተጠቃሽ ሆነዋል።

በሌላ ወገን ተሰልፈዋል በሚል በመረጃ ምንጮች የሚጠቀሱት በአቶ ስብሃት ነጋ የሚመራ ሲሆን፣ አቶ አባይ ጸሃዬ ተጠቃሽ ሆነዋል የደህንነት ዋና ሃላፊው አቶ ጌታቸው ከዚሁ ቡድን ጋር በመሆን ለቡድኑ የጥበቃና የመረጃ ሽፋን እንደሚሰጠው ተመልክቷል። ዶ/ር ጸብረፅዮን ገ/ሚካዔል አርከበ ዕቁባይ አሰላለፋቸው እስካሁን በውል እንዳልለየ ተመልክቷል።