ሙስሊሞችና ክርስቲያኖች የተሳተፉበት የስልክ ጥሪ ማቆም አድማ ተካሄደ

የካቲት ፳(ሃያ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ሰሞኑን እንዳዲስ ተጠናክሮ በቀጠለው ሙስሊም ኢትዮጵያውያንን የማሰር ዘመቻውን በመቃወም ድምጻችን ይሰማ የጠራው ስልክን ለ12 ሰአታት የማጥፋት ዘመቻ በተሳካ ሁኔታ መካሄዱን ዘጋቢያችን ገልጿል፡፡

በርካታ ሙስሊሞች ስልኮቻቸውን አጥፍተው የዋሉ ሲሆን፣ በማህበራዊ የመገናኛ ብዙሃን የሚያደርጉትን እንቅስቃሴም አቁመው ውለዋል። በርካታ ክርስቲያኖችም ጥሪውን ደግፈው ስልካቸውን ዘግተው ውለዋል።

እርምጃ የመንግስት ዋነኛ የገቢ ምንጭ በሆነው ቴሌ ላይ የኢኮኖሚ ጉዳት  ለማድረስ ታቅዶ የተተገበረ ነው።