“ፍርዱን ተፈጻሚ አድርጉትና ሰው እየሳቀ እንደሚሞት ላሳያችሁ እያልኩ ደህንነቱን ጠይቄያቸዋለሁ” ሲሉ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ተናገሩ

“ፍርዱን ተፈጻሚ አድርጉትና ሰው እየሳቀ እንደሚሞት ላሳያችሁ እያልኩ ደህንነቱን ጠይቄያቸዋለሁ” ሲሉ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ተናገሩ
(ኢሳት ዜና ግንቦት 21 ቀን 2010 ዓ/ም) ዛሬ ከእስር ተለቀው ከቤተሰቦቻቸው እና ከደጋፊዎቻቸው ጋር የተገናኙት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ፣ ደህንነቶች ምርምራ ቢያመደርጉበት ወቅት፣ በእንዲህ አይነት አገር ከምኖር ፍርድ ቤት የወሰነውን የሞት ፍርድ ቤት ፈርዳችሁ እንድትገድሉኝ፣ ዛሬም እዚህ ቁጭ ብዬ የምናገረው ፍርድ ቤት የወሰነውን ውሳኔ በአስቸኳይ እንዲወስኑ ነው። ሰው እየሳቀ ሊሞት እንደሚችል አሳያችሁዋለሁ።” ብለው እንደተናገሩና በቴለቪዥን ቆራርጠው እንዳቀረቡባቸው ተናግረዋል።
አቶ አንዳርጋቸው ፣ ዛሬ ተፈትቻለሁ፣ ግን ብዙ ያልተፈቱ ጉዳዮች አሉ፣ ቀኑ የደስታ ቀን ነው፣ ግን ቀኑ የደስታ ብቻ ሳይሆን በእናንተ ውስጥ ያለውን ስሜት እንዴት ነው ወደ ተሻለ ሁኔታ የምንቀይረው የሚለው ዋናው ነገር ነው ብለዋል። አራት አመት ብዙ መስዋትነት የተከፈለበት ሊመስላችሁ ይችላል፣ ግን መስዋትነቱ ትንሽ ነው። የዚህ አገር ችግር ለመፍታት ብዙ መስዋትነት ይጠይቃል ብለዋል፡
አቶ አንዳርጋቸው ፣ በአረብ አገር ተሰደው ስቃይ የተፈጸመባቸው የኢትዮጵያ ሴቶች ላይ የደረሰው ግፍ በስልጣን ላይ ባሉት ገዢዎች ላይ ጠንካራ ንግግር እንዲናገሩ እንዳደረጋቸው ይህም ጥያቄ በደህንነቶች ይቀርብላቸው እንደነበር ተናግረዋል።
የአርበኞች ግንቦት7 ሊ/መንበር ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ በበኩላቸው ፣ እንደማንኛውም ኢትዮጵያዊ እንደ ትግል ጓደኛዬ በመፈታቱ በጣም ደስ ብሎኛል፣ ዋናው ከዚህ በሁዋላ እሱ የታሰረለት ሁላችንም የምንታገልለት አላማ አገሪቱን ዲሞክራሲያዊ ለማድረግ ነው፣ እሱም የሚፈልገው ይህንን ነው ብለዋል።
ለአቶ አንዳርጋቸው የተደረገው አቀባበል ምን ያሳያል ተብለው የተጠየቁት ፕ/ር ብርሃኑ፣ ህዝቡ ለአቶ አንዳርጋቸው ያላቸውን ፍቅር ከመግለጽ በተጨማሪ ህዝቡ ፍትህ ፣ ዲሞክራሲና ነጻነት የጠማው መሆኑን የሚያሳይ ነው ብለዋል።
በዝግጀቱ ላይ ተገኝተው አስተ|ያየታቸውን ከሰጡት መካከል ወ/ት እየሩሳሌም ተስፋውን አነጋግረናታል።