የአቡነ ጳውሎስ ዜና እረፍት የተደበላለቀ ስሜት ፈጥረ

ነሀሴ ፲ (አስር) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም

ኢሳት ዜና:-ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ጻውሎስ ፓትሪያሪክ ርዕሰ ሊቀጻጻስት ዘኢትዮጵያ ሊቀጻጻሳት ዘአክሱም ወጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ፣የዓለም አብያተክርስቲያናት ፕሬዚዳንት በ76 ዓመታቸው አርፈዋል።

20ኛ ዓመት የሲመት በዓላቸውን ሐምሌ 5 ቀን 2004 ዓ.ም በሸራተን ሆቴል ያከበሩት አቡነ ጻውሎስ በባልቻ ሆስፒታል በሕክምና ሲረዱ ቆይተው ትላንት ለሊት አርፈዋል።

ኢትዮጵያውያን በተለይ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች በጳጳሱ ዜና እረፍት የተደበላለቀ ስሜት ተስምቷቸዋል። የአዲስ አበባ እና የክልል ከተሞች ዘጋቢዎቻችን እንዳሉት ህዝቡ በዜና እረፍታቸው ባገኘው አጋጣሚ ሁሉ ሲነጋገር ውሎአል።

የአዲስ አበባው ወኪላችን ከቤተክህነት እና ከጳጳሱ ጽህፈት ቤት ካሉ የዜና ምንጮች ባገኘው መረጃ ጳጳሱ ሰሞኑን በጸና ታመዋል ተብሎ የተወራው ሀሰት ሲሆን፣ እንደዘወትራቸው ያሉባቸው የጤና መቃወሶችን ተቋቁመው መደበኛ ስራቸውን ሲያከናውኑ የነበሩና የፍስለታ ጾምን በቅድስተ ማርያም ቤተክርስቲያን ጸሎት በመምራትና ቡራኬ በመስጠት ሲያገለግሉ የነበረ ሲሆን እስከ ማክሰኞ ድረስ ጸሎት በመምራት ሲቀድሱና ሲያስቀድሱ ነበር።

ይሁን እንጅ ማክሰኞ እለት ጸሎት ሲመሩ እየተዳከሙና ድምጻቸው የቀነሰ ሲሆን ወደ ህክምና ተቋማት ተወስደው እርዳታ ቢደረግላቸውም ትላንት ሌሊት አርፈዋል::

የአቡኑን እረፍት ተከትሎ የፌደራል ጉዳዮች ጽህፈት ቤት እና አቶ አባይ ጸሀየ በዚህ ጉዳይ ላይ ከቤተክርስቲያኑዋ የበላይ ሀላፊዎች ጋር እየሰሩ መሆኑን ለማወቅ ተችሎአል።

አቡነ ጳውሎስ በቅርቡ 20 አመት የስልጣን ዘመናቸውን ድል ባለ ግብዣ በሸራተን ሲያከብሩ፣ በአቡኑ ጽህፈት ቤት ዋና በር ላይ ደግሞ ስኬታማ 20 አመታት የሚል ቢል ቦርድ ተሰቅሎአል።

____________________________________________________________________________________________________________________________________

ESAT is the first independent Ethiopian satellite service tasked to produce accurate and balanced news and information, as well as other entertainment, sports and cultural programming created for and by Ethiopians.

ESAT is committed to the highest standards of broadcast journalism and programming and will strive to provide an outlet of expression to all segments of the diverse Ethiopian community worldwide