የኢትዮጵያ ጦር ከሶማሊያ ለቆ ሊወጣ ነው

መጋቢት ፲፬ (አስራ አራት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም  ኢሳት ዜና:-የኢትዮጵያ ጦር ሰሞኑን ሁድሩ ከምትባለዋ የሶማሊያ ከተማ መልቀቁን ተከትሎ ባይደዋንና ሌሎች አካባቢዎችን በመተው ሙሉ በሙሉ ከሶማሊያ ሊወጣ ይችላል የሚለው መላምት አይሏል። የአፍሪካ ህብረት የሰላም አስከባሪ ሀይል የኢትዮጵያ ጦር አገሪቱን ለቆ ከወጣ የአልሸባብን ጦር ለመቋቋም እንደማይችል እየተነገረ ነው። የህብረቱ የሰላም አስከባሪ ሀይል አዛዥ የሆኑት አንድሪው ጉቲ ህብረቱ ሀይሉን እየገመገመ መሆኑን ተናግረዋል። አልሸባብ የኢትዮጵያ ...

Read More »

ደቡብ ሱዳን ሰሜን ሱዳን ከአወዛጋቢው ከተማ ጦሩዋን አላስወጣችም ስትል ከሰሰች

መጋቢት ፲፬ (አስራ አራት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም  ኢሳት ዜና:-የአገሪቱ የመከላከያ ሚኒሰትር ጆን ኑዩዎን እንደገለጡት በአዲስ አበባ በተፈረመው ስምምነት መሰረት፣ ደቡብ ሱዳን ጦሩን ሙሉ በሙሉ ከአወዛጋቢው የድንበር አካባቢ ብታወጣም ሰሜን ሱዳን ግን ጦሩዋን እስካሁን አላንቀሳቀሰችም። ሚኒሰትሩ በአካባቢው የሰፈረው የተመድ የሰላም አስከባሪ ሀይል ሱዳን ጦሩዋን ለምን እንዳለስወጣች መጠየቅ አለበት ብለዋል። በሁለቱ አገሮች መካከል የተነሳው ውዝግብ ከዛሬ ነገ መቋጫ ያገኛል ተብሎ ቢጠበቅም እስካሁን ...

Read More »

በደቡብ ክልል ለአቤቱታ የመጡ ዜጎች ታገቱ

መጋቢት ፲፫ (አስራ ሦስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም  ኢሳት ዜና:-የተለያዩ የመብት ጥያቄዎችን ለመጠየቅ በደቡብ ክልል በቁጫ ወረዳ ለአቤቱታ የወጡ ከ1000 ያላሱ ሰዎች በፖሊስ ታግተው መዋላቸውን የአካባቢው ሰዎች ለኢሳት ተናግረዋል። ከፍትህ ፣ ከመልካም አስተዳዳር እና ከመብት ጋር በተያያዘ በርካታ ጥያቄዎችን ላለፉት 8 አመታት ሲያቀርቡ የቆዩት የቁጫ ወረዳ ነዋሪዎች ፣ 7 ወኪሎቻቸው መታሰራቸውን በመቃወም ትናንት አቤቱታ ለማቅረብ ሲሰባሰቡ በፌደራል ፖሊሶች ታግተዋል። የታሰሩና ድበደባ ...

Read More »

በአንዋር መስኪድ ከፍተኛ የጸጥታ ጥበቃ መካሄዱ ታወቀ

መጋቢት ፲፫ (አስራ ሦስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም  ኢሳት ዜና:-በዛሬው እለት በአንዋር መስጊድ ከስግደት በሁዋላ የተለመደው መንግስትን የመቃወም ትይንት ይካሄዳል ብሎ የሰጋው ኢህአዴግ  በርካታ የአዲስ አበባ፣ የፌደራል ፖሊሶችን እና የደህንነት ሀይሎችን ቢያሰማራም ህዝቡ ስግደቱን አካሂዶ በሰላም ተበትኖአል። ፖሊሶች ተቃውሞ ይደረጋል የሚል መረጃ በማግኘታቸው በርካቶች የአድማ በታኝ ልብሶችን ለብሰው በትልልቅ መኪኖች ውስጥ ሆነው ትእዛዝ ይጠብቁ እንደነበር የአዲስ አበባው ዘጋቢያችን ገልጿል። ከትናትን ማታ ...

Read More »

ኢህአዴግ ከ700 በላይ የጎዳና ተዳዳሪዎችን ሰብስቦ ቅስቀሳ አደረገ

መጋቢት ፲፫ (አስራ ሦስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም  ኢሳት ዜና:-ትናንት ሀሙስ መጋቢት 12 ቀን 2005 ዓም የኢህአዴግ መንግስት ከ740 በላይ የጎዳና ላይ ተዳዳሪዎችን ስድስት ኪሎ በሚገኘው ስብሰባ ማእከል ለአንድ ሙሉ ቀን በመሰብሰብ በመጪው የአዲስ አበባና አካባቢ ምርጫ ኢህአዴግን እንዲመርጡ ቀስቅሷል። ለእያንዳንዱ ተሳታፊ 100 ብር ከመስጠት በተጨማሪ  የምሳ፣ የቡና እና የሻሂ ግብዣም አድርጓል። የጎዳና ተዳዳሪዎች ትናንት 2፡30 ላይ ነጭ ቲሸርት ለብሰው እና ...

Read More »

በኢትዮጵያ 8 በመቶ የሚሆኑ ህጻናት ብቻ ንጽህናቸው እንደሚጠበቅላቸው ዩኒሴፍ አስታወቀ

መጋቢት ፲፫ (አስራ ሦስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም  ኢሳት ዜና:-ድርጅቱ የአለም የውሀ ቀንን ምክንያት በማድረግ ባወጣው መግለጫ በኢትዮጵያ ከአምስት አመት በታች ያሉ ህጸናት በአብዛኛው ከውሀ ንጽህና ጋር በተያያዘ እንደሚሞቱ ገልጿል። በኢትዮጵያ የዩኔሴፍ የአስቸኳይና የመስክ ጥናት ቡድን ሀላፊ የሆኑት ሳንጃይ ዊስኬራ ሲናገሩ ” ቁጥሮችን ስንጠቅስ ትክክለኛውን የህጻናትን ፊት ማየት አለብን፣ አንዳንድ ጊዜ በትልልቅ ቁጥሮች ላይ እናተኩራለን፣ ከእነዚህ ትልልቅ ቁጥሮች ጀርባ ስለሚያልቁት ሰዎች ...

Read More »

ከአምስት ዓመት በፊት በሕግ የፈረሰውን የኢትዮጽያ ዜና አገልግሎት ድርጅት እንደገና ወደነበረበት ለመመለስ ዕቅድ መኖሩን ምንጮች ጠቆሙ

መጋቢት ፲፫ (አስራ ሦስት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም  ኢሳት ዜና:-የቀድሞ ማስታወቂያ ሚኒስቴርን መፍረስ ተከትሎ ግልጽ ባልሆነ ምክንያት እንዲፈርስ የተደረገው የቀድሞ መንግስታዊ ዜና አገልግሎት በአሁኑ ወቅት በአቶ በረከት ስምኦን በሚመራው የመንግስት ኮምኒኬሽን ጽ/ቤት በአንድ መምሪያ ስር በሕግ ባልተሰጠው ስም “የኢትዮጽያ ዜና አገልግሎት-ኢዜአ” በሚል ዜናዎችን በመስራት ለመንግስት መገናኛ ብዙሃን በመሸጥ ላይ መገኘቱ ብዙዎችን ግራ የሚያጋባ ሆኗል፡፡ የመንግስት ኮምኒኬሽን ጽ/ቤት እያካሄደ ባለው የሪፎርም ስራ ...

Read More »

በአፋር ህጻነት በርሀብ እየረገፉ ነው

መጋቢት ፲፪ (አስራ ሁለት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም  ኢሳት ዜና:-በክልሉ ካለፉት አራት ወራት ጀምሮ የተከሰተው ከፍተኛ ረሀብና የውሀ እጥረት የበርካታ ህጻናትን ህይወት መቅጠፉን ነዋሪዎች ለኢሳት ገልጸዋል። ምንም እንኳ 60 በመቶ በሚሆነው የአፋር አካባቢ ከፍተኛ የሆነ የምግብና የውሀ እጥረት ቢከሰተም ፣ ችግሩ ከሁሉም ወረዳዎች አስከፊ ሆኖ በቀጠለበት የእዳ ወረዳ 6 ህጻናት በአንድ ወር ውስጥ ሞተዋል። ይህ አሀዝ በአንድ ሰፈር ብቻ የተጠናከረ እንጅ ...

Read More »

የኢህአዴግ አባል ድርጅቶች በአብዛኛው ነባር አመራሮቻቸው በስራ አስፈጻሚነት ቀጠሉ

መጋቢት ፲፪ (አስራ ሁለት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም  ኢሳት ዜና:-የኢህአዴግ አባል ድርጅቶች ሰሞኑን በተከታታይ ባካሄዱዋቸውና በመተካካት ረገድ እምብዛም ለውጥ ያልታየባቸው ጉባዔዎች በአብዛኛው ነባር አመራሩን ይዘው ሲያስቀጥሉ መጠነኛ የሆነ እርምጃም ወስደዋል፡፡ በዚሁ መሰረት ኦህዴድ አቶ አባዱላ ገመዳን፣ ግርማ ብሩን እና ኩማ ደመቅሳን ከስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባልነት ሲያሰናብት፤ ብአዴን በበኩሉ የፍትህ ሚኒስትር የሆኑትን አቶ ብርሃን ኃይሉን፣ደኢህዴን ደግሞ አቶ ተሾመ ቶጋን አሰናብቷል፡፡ ብአዴን በጤና ...

Read More »

ኢትዮጵያውያን በጄኔቭ የተቃውሞ ሰልፍ አደረጉ

መጋቢት ፲፪ (አስራ ሁለት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም  ኢሳት ዜና:-ኢትዮጵያውያኑ ትናንት ባደረጉት የተቃውሞ ሰልፍ ገዢው ፓርቲ በሙስሊም ኢትዮጵያውያን ጥያቄ ዙሪያ የየዘውን አቋም ከማውገዝ ባለፈ፣ በአገረቱ ውስጥ የሰብአዊ መብቶች ጥሰት እየተባባሰ መምጣቱን ለተባበሩት መንግስታት ድርጅቶች የተለያዩ ክፍሎች አስታውቀዋል። የሰላማዊ ሰልፉ አስተባባሪ ፣ የቢላል ኮሚቴ መስራችና ዋና ጸሀፊ የሆኑት አቶ ኤልያስ ረሺድ ከኢሳት ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ አንደገለጡት ሰላማዊ ሰልፉ  ሙስሊም ኢትዮጵያን የሚያደርጉትን  ትግል ...

Read More »