የአውሮፓ ህብረት ኢትዮጵያውያን ለመብታቸው መከበር የሚያሰሙትን ድምጽ ይሰማል ሲሉ ወ/ሮ አና ጎሜዝ ተናገሩ

ሰኔ ፲፪ (አስራ ሁለት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:- የአውሮፓ ህብረት ፓርላማ አባል የሆኑት እና በምርጫ 97  ወቅት የህብረቱ የምርጫ ታዛቢ ቡድን መሪ  የነበሩት ወ/ሮ አና ማርያ ጎሜዝ ይህን የተናገሩት ኢትዮጵያውያን ዛሬ በአውሮፓ ህብረት መቀመጫ ፊትለፊት  ባደረጉት የተቃውሞ ሰልፍ ላይ  ነው ። ወ/ሮ አና ጎሜዝ የአውሮፓ ህብረት የኢትዮጵያውንን ጩሀት ሰምቶ መልስ እንደሚሰጥ  ተናግረው፣ በግላቸው ከኢትዮጵያውያን ጎን ቆመው  ለውጥ እስከሚመጣ  እንደሚታገሉ ...

Read More »

በኢትዮጵያ ከፍተኛውን ኢንቨስተር መንግስት ነው ሲል የአለም ባንክ አስታወቀ

ሰኔ ፲፪ (አስራ ሁለት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:- ባንኩ  በገንዘብና የ ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር አነሳሽነት ያጠናቀረውን ሪፖርት  በሸራተን አዲስ ይፋ ሲያደርግ የኢትዮጵያ መንግሥት በዓለም በከፍተኛ መጠን ኢንቨስት ያደርጋሉ ከሚባሉ ሦስት መንግሥታት መካከል  እንደሆነ ፤በ አንፃሩበግል ዘርፉ የሚካሄደው   ኢንቨስትመንት የ ኣለማችን ስስድስተኛው ዝቅተኛ  ኢንቨስትመንት መሆኑን አመልክቷል፡፡ እንደ ሪፖርተረ  ዘገባ፤ የባንኩ የኢትዮጵያ ዳይሬክተር ጉዋንግ ቼንግና የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስትር ዴኤታው ዶ/ር ...

Read More »

በአማራ ክልል ከ493 ሺ በላይ ሄክታር መሬት ደን እየወደመነ ተባለ፣ ክልሉ ግን አስተባብሎአል።

ሰኔ ፲፪ (አስራ ሁለት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:- በደብረ ማርቆስ የየራባ ደን ፤በአዊ ዞን እንጅባራ የገንብሃ ጫካ ፤በደብረ ታቦር እና በኮምቦልቻም አመታትን ያስቆጠሩ ደኖች እየጠመነጠሩ መሆኑን የአካባቢው ነዋሪዎች ለኢሳት ገልጸዋል፡፡ ከፍተኛ የደን ቆረጣ በሚካሄድባቸው በአዊ እና በደብረማርቆስ አካባቢዎች ነዋሪዎች ቅሬታቸውን እያሰሙ ነው። ብዛታቸው ያልታወቀ ጥቁር ዝንጀሮ፣ ጅብ፣ ከርከሮ፣ ድፈርሳ፣ ትልልቅ ጥንቸሎች፣ አረንጓዴ ልባስና ቀይ መንቁር ያላቸው ወፎች፣ የሐበሻ ነብር ...

Read More »

በአዲስ አበባ ከተማ የጉለሌና አራዳ ክፍለ ከተማ ነዋሪዎች ከፍተኛ የውሃ እጥረት እንዳጋጠማቸው ገለጹ።

ሰኔ ፲፪ (አስራ ሁለት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:- የአዲሱ ገበያና የቀጨኔ አካባቢ ነዋሪዎች  የውሃ እጥረቱ ለኢኮኖሚና ለጤና ቀውስ እንደዳረጋቸው ተናግረዋል። በዚህ ዓመት  በተደጋጋሚ ከአንድ ወር በላይ የቆየ የውሃ እጥረት እንዳጋጠማቸው ነዋሪዎቹ ገልጸዋል። መንግስት ” የአራዳና ጉለሌ ክፍለ ከተሞች የቦታ አቀማመጥ ለውሃ ሥርጭቱ አመቺ አለመሆን፣ በእነዚህ ክፍለ ከተሞች ከፍተኛ የሕዝብ ቁጥር መጨመር ፣ በተለያዩ የልማት ሥራዎች ምክንያት የውሃ መስመሮች መሰበርና ...

Read More »

ማእከላዊ አፍሪካን ሪፑብሊክን በማሸነፍ የኢትዮጵያን ታሪክ እንደምንቀይረው አልጠራጠርም ሲል ምንያህል ተሾመ ተናገረ

ሰኔ ፲፪ (አስራ ሁለት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:- ምን ያህል ለኢሳት እንደገለጸው በተፈጠረው ነገር በእጅጉ አዝኗል። እኔ በአገሬ ላይ አውቄ እንዲህ አይነት ነገር አልሰራም ያለው ምንያህል፣ ቢጫ ካርድ ከተሰጠው ከ10 ወራት በሁዋላ ብዙ ጨዋታዎችን መጫወቱ ቢጫ ማግኘቱን እንዲዘነጋ እንዳደረገው  ገልጿል። የሚመለከታቸው የስፖርቱ ሀላፊዎች “ሁለት ቢጫ ካርዶችን ማየትክን  አልነገሩህም ነበር? ተብሎ ለተጠየቀው ደግሞ  አንድ ቢጫ ብቻ እንዳለኝና ከደቡብ አፍሪካ ጋር ...

Read More »

ግብጽና ኢትዮጵያ የቃላት ጦርነቱን ለመቀነስ ተስማሙ

ሰኔ ፲፩ (አስራ አንድ) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የሁለቱ አገሮች የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች በሰጡት መግለጫ አገራቱ የቃላት ጦርነቱን አቀዝቅዘው የኤክስፐርቶች ቡድን በቅርቡ በሰጠው አስተያየት ላይ ተጨማሪ ውይይት እንዲያደርጉ ተስማምተዋል። የኢትዮጵያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሀኖም፣ በአባይ ላይ አብረን መዋኘት ካልቻልን ተያይዘን እንሰምጣለን ብለዋል። በውይይቱ መሀልም ሱዳንን ለማካተት ተስማምተዋል። በውይይቱ አንድ ስምምነት ላይ እስከሚደረስ ድረስ ኢትዮጵያ የግድቡን ግንባታ ለማቆም  መስማማት ...

Read More »

የኢትዮጵያ የውጭ ምርቶች ዋጋ ቅናሽ እያሳየ ነው

ሰኔ ፲፩ (አስራ አንድ) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-እየተገባደደ ባለው የኢትዮጵያዊያን የ2005 በጀት ዓመት ዘጠኝ ወራት ማለትም ከሐምሌ 1/ 2004 እስከ መጋቢት 30/ 2005 ዓ.ም ባሉት ጊዜያት ዋናዎቹ የወጪ ንግድ ምርቶች በዓለም ገበያ ገቢያቸው ማሽቆልቆሉን ከገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን የተገኘ መረጃ ጠቁሟል፡፡ በተጠቀሰው ጊዜያት 2 ነጥብ 2 ቢሊየን የአሜሪካን ዶላር የተገኘ ሲሆን ይህ ገንዘብ ከአምና ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር በ5 በመቶ ...

Read More »

ኢህአዴግ የዲያስፖራ ፖሊሲውን ተግባራዊ ለማድረግ እንቅስቃሴውን ቀጥሎአል

ሰኔ ፲፩ (አስራ አንድ) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የኢሕአዴግ መንግስት ዲያስፖራውን የስርዓቱ ደጋፊ  ለማድረግ የቀየሰውን ስትራቴጂ ተግባራዊ ለማድረግ  በቅርቡ ከተለያዩ አህጉራት ከሄዱ የዲያስፖራ አባላት ጋር እየመከረ ሲሆን፣ ዲያስፖራው በአገር ውስጥ ስለሚያገኛቸው ጥቅሞች ገለጻ እየተደረገለት ነው። ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ቴዎድሮስ አድሃኖምን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት በተገኙበት በሚልንየም አዳራሽ በተካሄደው ስብሰባ ላይ ነዋሪነታቸው በውጭ አገር የሆኑ  የስርዓቱ ደጋፊዎች መገኘታቸው የታወቀ ሲሆን ጠቅላላ ...

Read More »

የኢትዮጵያ እና የግብጽ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ተወያዩ

ሰኔ ፲ (አስር) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:- የኢትዮጵያና የግብጽ ፍጥጫ እያየለ መምጣቱን ተከትሎ የግብጽ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር የሆኑት ሞሀመድ ካሚል በአዲስ አበባ ከኢትዮጵያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሀኖም ጋር ተነጋግረዋል። ሬዲዮ ፋና ባቀረበው የቀን ዘገባ ላይ  የሁለቱ አገራት ባለስልጣናት ባደረጉት የማለዳው ውይይት ከስምምነት ላይ ሳይደርሱ መቅረታቸውን ገልጿል። ሬዲዮ ፋናም ሁለቱ ባለስልጣኖች ስምምነት ላይ አልደረሱም የሚል ዜና ይፋ ካደረገ ...

Read More »

በአፋር የገዋኔ ነዋሪዎችና በፌደራል ፖሊሶች መካከል ያለው ውዝግብ እንደቀጠለ ነው

ሰኔ ፲ (አስር) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና:- ትናንት ገዋኔ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ አንድ ሾፌር መገደሉን ተከትሎ በፖሊሶች እና በነዋሪዎች መካከል አዲስ ውዝግብ ተከስቷል። በአካባቢው የተሰማሩት የፌደራል ፖሊስ አባላት ለሹፌሩ መገደል የገዋኔ ነዋሪዎችን ተጠያቂ አድርገዋል። ነዋሪዎቹ በበኩላቸው ግድያውን የፈጸሙት እነሱ አለመሆናቸውን  የዞኑ አስተዳዳሪ አቶ ሀይሰማ ወልዶ እና ሌሎች ሁለት የፌደራል ፖሊስ አዛዦች በተገኙበት ተናግረዋል። ነዋሪዎቹ “የፌደራል ፖሊስ አባላት ሶስት ጊዜ ...

Read More »