የአዲስ አበባ ፖሊሶች የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችንና ደጋፊዎችን ለማስፈራራት ሙከራ እያደረጉ ነው

ሚያዚያ ፲፯ (አስራ ሰባት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በመጪው እሁድ በጃንሜዳ ለሚካሄደው የተቃውሞ ሰልፍ የአዲስ አበባ መስተዳድር እውቅና ቢሰጥም ፣ የአዲስ አበባ መስተዳድር ፖሊሶች ህዝቡ በብዛት እንዳይገኝ ለማድረግ የማስፈራሪያ እርምጃ እየወሰዱ መሆኑን የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ወጣት ብርሃኑ ተክለ ያሬድ ገልጿል። ወጣት ብርሃኑ እንዳለው የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽነር በሰልፉ ላይ አንድም ነገር ቢከሰት እንዲሁም ከተሰጣችሁ ጊዜ አንድ ማይክሮ ሰከንድ ብታልፉ ...

Read More »

የደቡብ ሱዳን ከፍተኛ ባለስልጣናት ከእስር ተለቀቁ

ሚያዚያ ፲፯ (አስራ ሰባት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የደቡብ ሱዳን መንግስት በአራት የቀድሞ ባለስልጣናት ላይ የከፈተውን የአገር ክዳት ወንጀል እንዲቆምመወሰኑን ተከትሎ፣ ባለስልጣኖቹ ከእስር ቤት ወጥተዋል። የደህንነት ሚኒስትሩ ኦያይ ደንግ አጃክ፤ የድርጅቱ ዋና ጸሃፈ  የነበሩት  ፓጋን  አሞም፤ የመከላከያ ሚኒስትር ማጀክ ደ አጎት አተም እና በአሜረካ የደቡብ ሱዳን አምባሳደር የነበሩት እዝቅኤል ሎል  ከእስር ቤት ሲወጡ በደጋፊዎቻቸው ከፍተኛ አቀባበል ተደርጎላቸዋል። መንግስት እርምጃው የተወሰደው ለሰላምና አገሩን ለማረጋጋት ...

Read More »

አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ የመንግስታቸውን የስራ አፈጻጸም ሪፖርት አቀረቡ

ሚያዚያ ፲፮ (አስራ ስድስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የመንግሥታቸውንየ2006 በጀትዓመትየዘጠኝወራትዕቅድአፈጻጸምበዛሬውዕለትለፓርላማያቀረቡትጠ/ሚኒስትርኃይለማርያምደሳለኝ፤የቀድሞጠ/ሚኒስትርአቶመለስዜናዊ “መሰዋት” ለኢኮኖሚዕድገቱፈታኝነበርብለዋል፡፡ ጠ/ሚኒስትሩበ2005 በጀትዓመት 11 በመቶዕድገትታስቦ 9.7 በመቶዕድገትመገኘቱንጠቅሰውዕድገቱ ከዕቅዱያነሰቢሆንምከሰሃራበታችያሉአገራትካስመዘገቡትየ5.4 በመቶዕድገትጋርሲነጻጸርእጅግከፍተኛነበርሲሉአወድሰዋል፡፡ በ2005 በጀትዓመትመጀመሪያየቀድሞጠ/ሚኒስትርአቶመለስዜናዊመሰዋትንተከትሎየነበረውየመቀዛቀዝሥጋትበዕድገቱላይአሉታዊተጽዕኖሊያሳድርየሚችልፈታኝሁኔታየነበረመሆኑይታወሳልብለዋል፡፡ ጠ/ሚኒስትሩበተለይየአቶመለስንተፈጥሮአዊሞትመሰዋዕትነትበማድረግየማቅረባቸውና  ሞታችውበአገርኢኮኖሚዕድገትላይአሉታዊተጽዕኖማሳረፉንመናገራቸው፣ሪፓርቱን በተከታተሉት የመዲናዋ ነዌረዎች ዘንድ ግንባሩየነበረውአንድሰውብቻነበርወይ?የሚልጥያቄ መፍጠን ዘጋብያችን አመልክቷል፡፡ በተጨማሪም 2005 ዓ.ምበዓለምገበያየቡናናየወርቅዋጋበከፍተኛደረጃያሽቆለቆለበትዓመትእንደነበርበሌላመልኩአገሪቱከውጪየምታስገባውየነዳጅምርቶችዋጋመጨመርአስቸጋሪ ሁኔታ ፈጥሮ እንደነበርጠቁመዋል፡፡ ከ2003 ዓ.ምጀምሮየተከሰተውንየዋጋንረትለማረጋጋትየተወሰዱእርምጃዎችአሉታዊተጽዕኖንእንዳያስከትሉበ2005 ዓ.ምከፍተኛጥንቃቄመደረጉንያስታወሱትጠ/ሚኃይለማርያምሆኖምጥንቃቄውስላመጣውውጤትሳይጠቅሱአልፈዋል፡፡ በተጨማሪምየትራንስፖርትናሎጀስቲክአገልግሎትንይበልጥቀልጣፋናውጤታማለማድረግሲባልሥራላይየዋለውየመልቲሞዳልሥርዓትበአቅምማነስምክንያትበወጪናበገቢንግድእናበኢኮኖሚእንቅስቃሴላይአሉታዊተጽዕኖፈጥሮየነበረመሆኑንምአምነዋል፡፡በ2006 በጀትዓመትዘጠኝወራትከወጪንግድየተገኘውየቡናኤክስፖርትበ25 በመቶቅናሽማሳየቱንአቶኃይለማርያምጠቅሰውበጠቅላላውየዘጠኝወራቱአፈጻጸምከዕቅዱአንጻርሲመዘንአፈጻጸሙ 63 በመቶያህልብቻመሆኑንአስታውቀዋል፡፡ አቶ ሃይለማርያም ከ5 አመቱ የእድገትና የትራንስፎርሜሽን እቅድ የተወሰኑትን ቀደም ብለው መሳካታቸውን አብዛኞቹን በቀሪው አንድ አመት ...

Read More »

የካሽ ሬጅስትራር እቅድ አለመሳካቱ ተገለጸ

ሚያዚያ ፲፮ (አስራ ስድስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የገቢዎችናጉምሩክባለስልጣንነጋዴዎችየሸያጭመመዝገቢያማሽኖችን (ካሽሬጂስተር) እንዲጠቀሙናበዚሁመሠረትየሚፈለግባቸውንግብርናታክስእንዲከፍሉበማሰብከተሸጡትመሳሪያዎችመካከልየሸያጭመረጃንወደመረጃቋትየሚልኩት 12 በመቶብቻመሆናቸውንዋናኦዲተርሰሞኑንለፓርላማውባቀረበውየ2005 የኦዲትሪፖርትአስታውቋል፡፡ የሸያጭመመዝገቢያመሳሪያዎችአገልግሎትላይመዋልከጀመሩበትከ2000 እስከ 2005 ዓ.ምባሉትጊዜያትለግብርከፋዩሕብረተሰብ 82 ሺ141 የሸያጭመመዝገቢያመሳሪያዎችየተሸጡሲሆንከዚህውስጥአገልግሎትላይየዋሉት 72 ሺ964 ወይንም 89 በመቶያህሉብቻናቸው፡፡ አገልግሎትላይከዋሉትመሳሪያዎችመካከል 8ሺ755 ወይንም 12 በመቶመረጃንወደ መረጃቋትየሚያስተላልፉሲሆንየተቀሩት 64 ሺ 209 ወይንም 88 በመቶመረጃን ወደ መረጃቋትየማያስተላልፉናቸውብሎአል፡፡ በተጨማሪም 5ሺ 888 ወይንም 12 በመቶያህልየሽያጭመመዝገቢያ መሳሪያዎችከሲስተሙጋርጨርሶያልተያያዙመሆናቸውንአስቀምጦአል፡፡ ባለስልጣኑበሸያጭመመዝገቢያመሳሪያየተመዘገቡየሽያጭመረጃዎችወደመረጃመረብቋትመተላለፍናአለመተላለፋቸውን ለማወቅ በየታክስማዕከሉምሆነበዋናውመ/ቤትደረጃክትትልናቁጥጥርማድረግየሚችልበትሥርዓትአለመዘርጋቱንዋናውኦዲተርአጋልጦአል፡፡ በተጨማሪምግብርከፋዩከሸያጭመመዝገቢያመሳሪያአቅራቢዎችገዝቶከሚጠቀምባቸውመሳሪዎችበአማካይበኣመት 15 ሺ 670 የሚሆኑትበብልሽትምክንያትለጥገናየሚገቡሲሆንከዚህውስጥ 46 በመቶውበ48 ሰዓታትእንደሚጠገኑ፣የተቀሩት ግን ሳይጠገኑ እንደሚከርሙየዋናውኦዲተርሪፖርትይጠቅሳል፡፡ የሽያጭመመዝገቢያመሳሪያዎቹበየኣመቱ ...

Read More »

የደቡብ ሱዳን ፕሬዘዳንት ሳልቫኪር የአገረቷን የጦር አዛዥ አባረሩ

ሚያዚያ ፲፮ (አስራ ስድስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ፕ/ት ሳልቫኪር ፣ ጄኔራል ጀምስ ሆት ማይን ለምን እንዳባረሩዋቸው ባይገልጹም የፖለቲካ ተንታኞች ግን  አማጽያኑ የቤንቲውን አካባቢ መቆጣጠራቸውን በምክንያትነት ይጠቅሳሉ። ከደቡብ ሱዳን የተፈናቀሉ በርካታ ዜጎች ወደ ኢትዮጵያ እየፈለሱ እንደሚገኙ የሚወጡት መረጃዎች ያመለክታሉ።

Read More »

በሰሜን ናይጄሪያ የሚገኝ እስላማዊ ፍርድ ቤት የ10 ዓመቷን ታዳጊ ወጣት በመድፈር በኤች አይ ቪ/ኤድስ ቫይረስ እንድትያዝ ያደረጋትን የ 63 ዓመት ጎልማሳ በድንጋይ ተወግሮ እንዲገደል ውሳኔ አሳለፈ።

ሚያዚያ ፲፮ (አስራ ስድስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አሶሲየትድ ፕሬስን በመጥቀስ ቢቢሲ እንደዘገበው ኢባሎ ሳይዱ ዶሳ የተባለው ተከሳሽ የ10 ኣመቷን ታዳጊ ወጣት እንደደፈረ ያመነ ሲሆን፤”ድርጊቱን የፈፀምኩት ሰይጣን አሣስቶኝ ነው ብሏል። ዾሳ ሁለት ሚስቶች የነበሩት ቢሆንም፤ሁለቱም ከኤች አይ ቪ/ኤድስ ጋር በተያያዘ ህመም  መሞታቸው ሪፖርት ተደርጓል። የሰሜን ናይጀሪያ እስላማዊ ፍርድ ቤት በበርካታ ተከሳሾች ላይ በድንጋይ ተወግረው እንዲሞቱ በተለያዩ ጊዜያት ፍርድ ያሳለፈ ቢሆንም፤ ...

Read More »

በሰመራ ከፍተኛ ተቃውሞ ተካሄደ

ሚያዚያ ፲፭ (አስራ አምስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአፋር ክልል መስተዳደር መቀመጫ ሰመራ ዛሬ በተካሄደው የተማሪዎች ተቃውሞ የልዩ ሃይል  አባላት በተማሪዎች ላይ ድበደባ ፈጽመዋል። ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ ተማሪዎች ተደብድበው ሆስፒታል ሲገቡ በርካታ ቁጥር ያላቸው ደግሞ ታስረዋል። የኮሌጅና የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች ጧት ላይ መኪኖችን አግደው ከዋሉ በሁዋላ ልዩ ሃይል በወሰደው እርምጃ እገታውን ቆሟል። ተማሪዎች ከሰአት በሁዋላ ወደ ክልሉ ጽህፈት ቤት በመሄድ ...

Read More »

የፌዴራልዋናኦዲተር በትምህርት ተቋማት፣ በውጭጉዳይና በመከላከያ ውስጥ ከፍተኛ የገንዘብ ጉድለት መኖሩን አመለከተ

ሚያዚያ ፲፭ (አስራ አምስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የመ/ቤቱዋናኦዲተርየሆኑትአቶገመቹዱቢሶየ2005 ዓ.ምየኦዲትሪፖርታቸውን ለፓርላማ ባቀረቡበት ወቅት  በ132 የመንግሥትመ/ቤቶችላይበተካሄደውኦዲትከፋይናንስሥርዓት፣ደንብናመመሪያጋር የሚጋጩበርካታግድፈቶችመታየታቸውንአመልክተዋል፡፡ የትምህርት ተቋማትና መከላከያ ከፍተኛ የገንዘብ ጉድለት ከተገኘባቸው መስሪያ ቤቶች መካከል በቀዳሚነት ተጠቅሰዋል። ዋናኦዲተሩባቀረቡትና 54 ያህል ገጾችንበያዘውበዚሁሪፖርታቸውሂሳብበወቅቱያለማወራረድችግር፣የተሟላየወጪማስረጃሳይቀርብበወጪ ተመዝግቦመገኘት፣ደንብናመመሪያሳይከተሉግዥዎችንመፈጸም፣የጥሬገንዘብጉድለቶች፣በብልጫየተከፈሉ ሂሳቦች፣ቀረጥተከፍሎባቸውገቢለመሆናቸውማስረጃያልቀረበባቸውሂሳቦች፣ከበጀትበላይወጪማውጣትና የመሳሰሉየሂሳብአሠራርግድፈቶችበበርካታመ/ቤቶች ታይተዋል፡፡ የጥሬ ገንዘብ ሂሳብ አያያዝና አጠባበቅ ትክክለኛነት ለማረጋገጥ ኦዲት ሲደረግ፤ በ5 መ/ቤቶች ብር 1 ሚሊዮን ,272,ሺ 93ብር ከ33 ሳንቲም የጥሬ ገንዘብ ጉድለት ሲገኝ፣  ጉድለት የተገኘባቸው ዩኒቨርስቲዎች ተብለው የተጠቀሱት ደግሞ ጂማ፣ ሰመራ፣ ወሎ፣ ባህርዳርና ጅጅጋ   ናቸው፡ በጉድለት የታየው የጥሬ ገንዘብ ሂሳብ ተገቢው እርምጃ ተወስዶ እንዲተካ ለየመ/ቤቶቹ በተላከው የስራ አመራር ሪፖርት ማሳሰባቸውን ዋና ኦዲተሩ አመልክተዋል። በበጀት ዓመቱ መጨረሻ በሂሳብ መግለጫ ሪፖርት የተደረገውና በቆጠራ የተገኘው ጥሬ ገንዘብ መካከል በ3 መ/ቤቶች  ማለትም ...

Read More »

ሰማያዊ ፓርቲ በመጪው እሁድ ለሚያደርገው የተቃውሞ ሰልፍ ቅስቀሳውን አጠናክሮ ቀጥሎአል

ሚያዚያ ፲፭ (አስራ አምስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ፓርቲው ሚያዝያ 19/2006 ዓ.ም ‹‹የተነጠቁመብቶቻችንእናስመልስ›› በሚልመሪቃልታላቅናደማቅሰላማዊሰልፍበጃንሜዳ የሚያካሂድ ሲሆን፣ የፓርቲው ወጣት አባላት ወደ ተለያዩ የአዲስ አበባ ቦታዎች እየዞሩ ከፍተኛ ቅስቀሳ በማድረግ ላይ ናቸው። ፓርቲው ከአሁን ቀደም የተለያዩ ጥያቄዎችን በማንሳት ምላሽ እንዲሰጣቸው ቢጠይቅም ጥያቄዎቹ ምላሽ ያልተሰጣቸው ከመሆኑም ባሻገር ጭራሹን እየተባባሱ በመምጣታቸውና ህዝብም እየተማረረ በመሆኑ ሰላማዊ ሰልፉን መጥራት እንዳስፈለገ ገልጿል። ፓርቲው መምህራንና ነጋዴዎች በሰልፉ ላይ ...

Read More »

የአፍረካ  ህብረት የመርማሪዎች  ቡድን  ወደ ደቡብ ሱዳን  መሄዱ ታወቀ::

ሚያዚያ ፲፭ (አስራ አምስት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአፍሪካ ህብረት የተሰየመ  በቀድሞ የናይጄረያ ፕሬዘዳንት ኦለሰንጎ  ኦበሳጆ የሚመራ የልኡካን ቡድን   ወደደቡብ ሱዳን ያመራ ሲሆን ስራውም በደቡብ ሱዳን የተፈጸመውን የሰብአዊ  መብት ጥሰት መመርመርና ለአፍሪካ ህብረት አስፈላጊውን የመፍተሄ ሃሳብ ማቅረብ ይሆናል:: የልዑካን ቡድኑ ፕረዜዳንት ሳልቫኪርንና የተቃዋሚውን መሪ  ሬክ ማቻርን እንደሚያነጋግር ሲታወቅ  በጦርነቱም ስቃይ የደረሰባቸውን ሰዎች እንደሚያነጋግር  ታውቋል:: ይህ በዚህ እያለ በዛሬው  እለት ፕሬዝዳንት  ሳልቫኬርና  በተቃዋሚው መሪ በሬክ ማቻር መካከል ይካሄዳል የተባለው ...

Read More »