በሰሜን ሸዋ ዞን ችግር ተፈጥሮባቸው የነበሩት አካባቢዎች እየተረጋጉ ነው

(ኢሳት ዲሲ–ሚያዚያ 2/2011)አማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ሰሞኑን ችግር ተፈጥሮባቸው የነበሩት አካባቢዎች እየተረጋጉ መሆኑን የክልሉ የሰላም ግንባታና የህዝብ ደህንነት ጉዳዮች ቢሮ ምክትል ሃላፊ ገለጹ። ምክትል ሃላፊው አቶ ገደቡ ሃይሉ እንደሚሉት በአካባቢዎቹ ዳግም ችግሮች እንዳይፈጠሩ የመከላከያ፣የክልሉ ልዩ ሃይልና ሰላም አስከባዊ ሃይሉ በጋራ በመስራት ላይ ናቸው። በአካባቢው ልዩ ኮማንድ ፖስትን ለማቋቋም ወደ አካባቢው የተላከ የክልሉ የጸጥታ ሃይል መኖሩንም ገልጸዋል። በአማራ ክልል ሰሜን ...

Read More »

በኢንጅነር ታከለ ኡማና በጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ መካከል ውይይት ተደረገ

(ኢሳት ዲሲ–መጋቢት 30/2011)በአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ ኢንጅነር ታከለ ኡማና በጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ መካከል ውይይት መደረጉ ተገለጸ። ራሱን የአዲስ አበባ ባላደራ ምክር ቤት በሚል የሚጠራው አካል ባወጣው መግለጫ  እንዳስታወቀው በሁለቱ ወገኖች መካከል የተደረገው ውይይት ልዩነቶችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት በመስማማት ተጠናቋል። በከተማዋ ህዝባዊ ስብሰባዎችን ለማድረግ ለጠየቀው የባልደራስ አመራር የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ ጥያቄውን በመቀበል አዎንታዊ ምላሽ መስጠታቸውን ምክር ቤቱ ገልጿል። ስምምነቱን ተከትሎም ...

Read More »

በአጣዬና ማጀቴ የተፈጠረውን ችግር መቆጣጠሩ ተገለጸ

(ኢሳት ዲሲ–መጋቢት 30/2011)በሰሜን ሸዋ አጣዬና ማጀቴ የተፈጠረውን ችግር መቆጣጠሩን የአማራ ክልል መንግስት አስታወቀ። የክልሉ ጸጥታና ሰላም ቢሮ ምክትል ሃላፊ ኮሎኔል አለበል አማረ ለኢሳት እንደገለጹት ባለፉት ሁለት ቀናት በተለያዩ የሰሜን ሸዋ ዞን አካባቢዎች ያለውን አለመረጋጋት በመቆጣጠር ሰላም እንዲሰፍን ተደርጓል። በዛሬው ዕለት የክልል የተለያዩ የጸጥታ ሃይሎች አካባቢዎችን የማረጋጋት ስራ እያከናወኑ መሆኑን የጠቀሱት ኮሎኔል አለበል አማረ ጥቃት የፈጸሙት ሃይሎች ወደ መጡበት አካባቢ መመለሳቸውን ...

Read More »

የዜጎችን ሰላም ለመጠበቅ ህጋዊና ተመጣጣኝ ርምጃ እንደሚወሰድ ተገለጸ

(ኢሳት ዲሲ–መጋቢት 30/2011) በሃገሪቱ የተከሰተውን የሰላም መደፍረስ ለማረጋጋትና የዜጎችን ሰላም ለመጠበቅ ህጋዊና ተመጣጣኝ ርምጃ እንደሚወሰድ  የብሔራዊ ደህንነት ምክር ቤት አስታወቀ። የፌደራልና የክልል የፀጥታ አስከባሪ ተቋማትም አስፈላጊውን ህጋዊና ተመጣጣኝ ርምጃ እንዲወስዱ ትዕዛዝ መተላለፉን ምክር ቤቱ ገልጿል። የመከላከያ ሰራዊት ግጭት በተከሰተባቸው የአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች በመግባት የማረጋጋት ስራ በማከናወን ላይ መሆኑንም ይፋ አድርጓል። ብሔራዊ የደህንነት ምክር ቤቱ በመላ ሃገሪቱ እየተስተዋሉ ያሉ የሰላም ...

Read More »

በማጀቴና አጣዬ በኦነግ ታጣቂዎች የተገደሉ ሰዎች የቀብር ስነስርዓት ተፈጸመ

(ኢሳት ዲሲ–መጋቢት 30/2011) በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ማጀቴና አጣዬ በኦነግ ታጣቂዎች የተገደሉ ሰዎች የቀብር ስነስርዓት በዛሬው ዕለት ተፈጸመ። የአካባቢው ነዋሪዎች  ከኦነግ ታጣቂዎች ጥቃት ሊሰነዘርብን ይችላል በሚል ስጋት ከስፍራው እየለቀቁ መሆናቸውን ኢሳት ያነጋገራቸው  ገልጸዋል። በአጣየ ከቅዳሜ ምሽት ጀምሮ ከባድ መሳሪዎች በያዙ የኦነግ ታጣቂዎች በተከፈተው ጥቃት 15 ነዋሪዎች መገደላቸው ተገልጿል። በአጣዬ በነበረው ጥቃት ምክንያት መንገዶች ተዘግተዋል። በጥቃቱ የቆሰሉ ሰዎችን ወደ ህክምና ማዕከላት ...

Read More »

የኢትዮጵያ ልኡካን ቡድን ናዝራዊት አበራን ሊጎበኝ ነው

(ኢሳት ዲሲ–መጋቢት 27/2011)አደገኛ አፅ በማዘዋወር ተጠርጥራ በቻይና እስር ላይ የምትገኘው ናዝራዊት አበራ በኢትጵያ ልዑክ በቀጣይ ማክሰኞ እንደምትጎበኝ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ አቶ ነቢያት ጌታቸው እንዳለው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የናዝራዊት አበራን ጉዳይ በትኩረት እየተከታተለው ይገኛል። በቻይና ጁዋንግ የሚገኘው የኢትዮጵያ ቆንስላም ናዝራዊት አበራን ለሶስት ጊዜያት እንደጎበኛት ቃል አቀባዩ ተናግረዋል። ቃል አቀባዩ የቻይና መንግስት እስካሁን ምንም አይነት ክስ እንዳልመሰረተም ገልጸዋል። ...

Read More »

የ40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ለባለ እድለኞች እንዳይተላለፉ ታገደ

(ኢሳት ዲሲ–መጋቢት 27/2011) የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ የፍትሐብሄር ችሎት በቅርቡ እጣ የወጣባቸው የ40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ለባለእድለኞች እንዳይተላለፉ አገደ፡፡ የጋራ መኖሪያ ቤቱን ለማግኘት ተመዝግበው 100 በመቶ የከፈሉ 98 ዜጎች ክስ መመስረታቸውን ተከትሎ የፍርድ ሂደቱ እስከሚጠናቀቅ ድረስ ለባለ እድለኞች እንዳይተላለፉ በችሎቱ ታግደዋል። ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር የቤቶቹን ዋጋ መቶ በመቶ በመክፈል ቅድሚያ ለማግኘት የገባነው ውል አለ ያሉ 98 ተመዝጋቢዎች ...

Read More »

የጸጥታና ደህንነት ተቋማት የአንድ ዓመት ክንውን ይፋ ሆነ

(ኢሳት ዲሲ–መጋቢት 27/2011) የኢትዮጵያ መንግስት የጸጥታና ደህንንት ተቋማትን የአንድ ዓመት ክንውን ይፋ አደረገ። በአራቱ የጸጥታና የደህንነት ተቋማት ላይ ስር ነቀል ማሻሻያ በመደረግ ላይ መሆኑን አስታውቋል። በዛሬው ዕለት ለሀገር ውስጥ ጋዜጠኞች መግለጫ የሰጡት የጠቅላይ ሚኒስትሩ የጸጥታና ደህንነት አማካሪ ሚኒስትር አቶ ተመስገን ሙሉነህ በማሻሻያው ተቋማቱ ኢትዮጵያዊ ቅርጽ እንዲኖራቸው ማድረግ ትኩረት ተሰጥቶበት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። የተልዕኮ ግልጽነት ሳይኖራቸው ህዝብ ላይ አፈናና ሲፈጽሙ የነበሩና ...

Read More »

በአፋር ገዋኔ የተነሳው ሕዝባዊ ተቃውሞ እንደቀጠለ ነው

(ኢሳት ዲሲ–መጋቢት 27/2011) በአፋር ገዋኔ የተነሳው ሕዝባዊ ተቃውሞ ከአዲስ አበባ ወደ ጅቡቲ፣ከጅቡቲ ወደ አዲስ አበባ የሚወስደውን መንገድ በመዝጋት መቀጠሉ ተሰማ። ወደ መቀሌ የሚጓዙ ተሽከርካሪዎችም እንዳይንቀሳቀሱ መደረጉን ነው ለኢሳት የደረሰው መረጃ የሚያመለክተው። የራሳችንን ሰላም በራሳችን እናስከብራለን በሚል የተነሱት የአፋር ወጣቶች በንጹሃን ላይ ግድያ የፈጸሙ የመከላከያ አካላት ለህግ የማይቀርቡ ከሆነ መንገዶችን የመዝጋቱ ርምጃ ተጥናክሮ ይቀጥላል ብለዋል። በአፋር ገናሌ የ15 አመቱ ወጣት በመከላከያ ...

Read More »

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለስኳር ኮርፖሬሽን ብድር እንዲሰጥ መንግስት ጠየቀ

(ኢሳት ዲሲ–መጋቢት 26/2011) የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለስኳር ኮርፖሬሽን ለውጭ ዕዳ መክፈያና ለፕሮጀክቶች ማስፈጸሚያ 13 ቢሊዮን ብር ብድር እንዲሰጥ መንግስት ጠየቀ ። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለስኳር ኮርፖሬሽን ለሚሰጠው ተጨማሪ ብድር መንግሥት ዋስትና እንደሚሰጥም አስታወቋል። ከሳምንት በፊት በገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ኢዮብ ተካለኝ ተፈርሞ በዋናነት ለኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ እንዲሁም በግልባጭ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ  ደብዳቤ መላኩን ሪፖርተር ዘግቧል፡፡ ስኳር ኮርፖሬሽን እየገነባቸው ከሚገኙት የስኳር ...

Read More »