መንግስት በእነ አቶ በቀለ ገርባ ላይ መስክሮችን አሰማ

ጥር 1 ቀን 2004 ዓም ኢሳት ዜና:-የኢህአዴግ መንግሥት የፌዴራል ዐቃቤ- ሕግ በነ በቀለ ገርባ በሽብርተኝነት ወንጀል በከሰሳቸው ዘጠኝ የኦሮሞ ተወላጆች ላይ ከቦረና ሞያሌ እና ከሰሜን ሸዋ ኦሮሚያ ዞን ያስመጣቸውን አባላቱ አዲስ አበባ ሆቴል አስቀምጦ የምስክርነት ቃል በማስጠናት ዋና የዐቃቤ ህግ ምስክሮች ያላቸውን 18 ሰዎች ትላንትና እና ዛሬ በዋለው ከፍተኛው ፍርድ ቤት ሦስተኛ ወንጀል ችሎት አቀርቧል፡፡ የተቀሩ ሰባት  የዐቃቤ ህግ ምስክሮችን፣ ...

Read More »

በአፋር ህዝብ ላይ የሚደርሰው በደል እንደጨመረ ነው ተባለ

ጥር 1 ቀን 2004 ዓም ኢሳት ዜና:-የአፋር ህዝብ ፓርቲ ባወጣው መግለጫ፣ አባቃላ እየተባለ በሚጠራው የማጎሪያ ካምፕ ውስጥ በርካታ የተቃዋሚ መሪ ዘመዶች እና መንግስትን የሚቃወሙ አፋሮች በብዛት እየታጎሩ ነው። ከ300 በላይ የሚሆኑት አፋሮች ላለፉት 2 አመታት ፍትህ አጥተው በእስር ላይ እንደሚገኙ ፓርቲው አስታውቋል። የአፋር ህዝብ ፓርቲ ዞን አንድ፣ ዞን ሁለትና ዞን ሶስት እየተባለ በሚጠራው አካባቢዎች አርብቶ አደሮችን እያፈናቀሉ መሆኑን ጠቅሶ፣ ይህን ...

Read More »

በፈረንሳይ ኣስገዶም ዮናታን (ኢስማኢል ኢብሳ )የተባለ ኢትዮጵያዊ በፖሊሶች ተደብድቦ መገደሉ ተሰማ

ጥር 1 ቀን 2004 ዓም ኢሳት ዜና:-በፈረንሳይ መዲና ልዩ ስሙ ካሌ እየተባለ በተለምዶ በሚጠራው ኣካባቢ ኣስገዶም ዮናታን (ኢስማኢል ኢብሳ )የተባለ ኢትዮጵያዊ በፖሊሶች ተደብድቦ መገደሉ ተሰማ ፡፡ ጋዜጠኛ ዘላለም ገብሬ ከአሜሪካ እንደዘገበው “ከፈረንሳይ ወደ እንግሊዝ ለመግባት ጥረት በማድረግ ላይ እያሉ በፈረንሳይ ፖሊሶች እና በኢትዮጵያኖች መካከል በተነሳው ኣለመግባባት አና በተፈጠረው ግብ ግብ  መሰረት ህይወቱ አልፎአል። ወጣት ከደረሰበት ጉዳት ህይወቱን ለመታደግ ወደ ሆስፒታል ...

Read More »

የኦፌዴንና የኦህኮ አመራሮች ፍርድ ቤት ቀረቡ

የኢህአዴግ መንግሥት በአሸባሪነት ወንጀል ክስ መስርቶ በእስር ላይ ካዋላቸው ስድስት ወር የተጠጋቸው የኦሮሞ ፌዴራሊስት ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ኦፌዴን) ፓርቲ እና የመድረክ የአመራር አባል የሆኑት አቶ በቀለ ገርባ እንዲሁም የኦሮሞ ህዝቦች ኮንግረንስ (ኦህኮ) ፓርቲ እና የመድረክ የአመራ አባል የሆኑት አቶ ኦልባና ሌሊሳ እና ሌሎች ሰባት የኦሮሞ ተወላጆች ዛሬ ታህሳስ 30 ቀን 2004 ዓ.ም  ከፍተኛው ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ሦስተኛ ወንጀል ችሎት ቀረቡ ...

Read More »

የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ፤የማልታ መንግስት ያሰራቸውን ከ50 በላይ ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን እንዲፈታ ጠየቀ

የንቅናቄው ዋና ስራ-አስፈፃሚ ዳይሬክተር አቶ ኦባንግ ሜቶ በማልታ ለተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽነር ለሚስተር ማሪዮ ፍሪጀሪ በፃፉት ደብዳቤ፤ ኢትዮጵያውኑ በእስር ላይ ረዘም ላለ ወራት መቆየታቸው  እጅግ እንዳሣሰባቸው ገልፀዋል። እንዲሁም በእስር ቤት ውስጥ ሳሉ በተለይ ከጤናቸው ጋር በተያያዘ እያጋጠሙዋቸው ላሉ ችግሮች በቂ የህክምና አገልግሎትና መድሀኒት ሊያገኙ አለመቻላቸውም ድርጅታቸውን እጅግ እንደሚያሣስበው አቶ ኦባንግ ገልጸዋል። አገራቸው ውስጥ በተፈጠረ ፖለቲካዊ ችግር ሳቢያ ወደ ...

Read More »

አንድነት ፓርቲን ወክለው በመድረክ ውስጥ የሚሳተፉ ሦስት አመራሮች ተመረጡ

አንድነት  ለኢሳት በላከው መግለጫ ፤ፓርቲው ሰሞኑን ባካሄደው ስብሰባ፤ የፖርቲው ሊቀ-መንበር ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ የመድረክ ሥራ አስፈጻሚ፣  ኢ/ር ዘለቀ ረዲ የመድረክ ሥራ አስፈጻሚና ህዝብ ግንኙነት፣ አቶ ተመስገን ዘውዴ ደግሞ  የመድረክ የውጪ ዘርፍ አባል ሆነው እንዲሰሩ   በሥራ አስፈጻሚው ተወስኗል።  ገዥው ፓርቲ አቶ አንዷለምን ጨምሮ ሌሎችን የፓርቲው አመራሮችና አባላት በማሰር ድርጅቱን ለማዳከምና ብሎም ለማጥፋት የተለያዩ ጫናዎች መፍጠሩን ቢቀጥልም፤ የፓርቲው እንቅስቃሴ ግን ከመቼውም ጊዜ በላይ ተጠናክሮ ...

Read More »

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ -ክርስቲያን ህንፃዎች ህገ-ወጥ ተብለው ፈረሱ

 ቤተ-ክርስቲያኒቱ ዳግማዊ ምኒልክ ፊት ለፊት በሚገኘው በተለምዶ ‹‹ጠጠር ሕንፃ›› በሚባለው ውስጥ የሚገኙ ልዩ ልዩ ግንባታዎቿ ሕገወጥ እየተባሉ እንዲፈርሱ መደረጋቸውን አጥብቃ ተቃወመች::  የአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ ዘጠኝ አስተዳደር መሰንበቻውን በቤተክህነት ሕንፃ ላይ ባካሄደው ዘመቻ፤ አምስት የንግድ ቤቶችንና መጋዘኖችን አፍርሷል::  እንደ ሪፖርተር ዘገባ፤ ከቤተክህነት ቤቶቹንና መጋዘኖቹን ተከራይተው ይሠሩ የነበሩ ነጋዴዎች ወረዳው የወሰደውን ዕርምጃ ሕጋዊነት የሌለው ሲሉ ከቤተክህነት ጋር በመሆን እየተቃወሙት ይገኛሉ::  ተቃውሞ ...

Read More »

ፔትሮናስ የተባለው የነዳጅ ኩባንያ አካባቢውን ለቆ ከወጣ በሁዋላ፣ ሳውዝ ዌስት ኢነርጂ የተባለ ሃገር በቀል ኩባንያ በጋምቤላ ክልል የነዳጅ ፍለጋ ሊያካሂድ ነው

በኩባንያው ድረገጽ ላይ ላይ የሰፈረው መረጃ እንደሚያሳየው፣ ሳውዝ ዌስት ኢነርጂ  በሚቀጥሉት አራት አመታት ውስጥ በክልሉ ነዳጅ ይገኝበታል ተብሎ የሚታመንበትን 17 ሺ ስኩዌር ኪሎ ሜትር ቦታን ተረክቦ ነዳጅ ያፈላልጋል። ፔትሮናስ ኩባንያ ቀደም ብሎ በክልሉ ነዳጅ የማፈላለግ ስራ ሲሰራ ቢቆይም ፣ በጸጥታ እና በቂ መርት የለም በሚል ሰበብ አካባቢውን ለቆ መውጣቱ ያታወሳል። ከፔትሮናስ በሁዋላ በጋምቤላ አካባቢ የነዳጅ ስራ ለማከናወን የደፈረ የውች አገር ...

Read More »

የጋምቤላ ርዕሰ መስተዳድር “መለስ ዜናዊ መታሰር አለባቸው አሉ”

ታህሳስ 28 ቀን 2004 ዓ/ ም ኢሳት ዜና:-የጋምቤላ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦሞት ኦባንግ አሎም “እኔ ከታሰርኩ መለስም ይታሰራል” በማለት በከፍተኛ የፌደራል ባለስልጣናት ፊት ተናግረዋል። ተባባሪ ዘጋቢያችን አሰግድ ተፈራ እንደዘገበው የፌደራል መንግስት ባለስልጣናት ርዕሰ መስተዳደሩን በአኝዋክ ንፁሃን ጭፍጨፋ ወቅት የሚገደሉትን ሰዎች ስም ዝርዝር አዘጋጅተው አቅርበዋል በሚል ክስ መስርተውባቸዋል። በክልሉ ነዋሪዎች “እውነተኛው ወያኔ” የሚል ስያሜ ያላቸው አቶ ኦሞት፣አቶ መለስ መታሰር አለባቸው በማለት ...

Read More »

ለዓባይ ግድብ መዋጮ ያለ ያለ ፍላጎቴ ከደመወዜ ተቆርጦብኛል ያሉ አንድ መምህር ክስ መመስረታቸውን አዲስ አድማስ ዘገበ

ታህሳስ 28 ቀን 2004 ዓ/ ም ኢሳት ዜና:-ለዓባይ ግድብ መዋጮ ያለ ያለ ፍላጎቴ ከደመወዜ ተቆርጦብኛል ያሉ አንድ መምህር ክስ መመስረታቸውን አዲስ አድማስ ዘገበ። በድል በትግል ትምህርት ቤት ለረዥም ዓመታት በመምህርነት ያገለገሉት አቶ ግርማ በፈቃዱ “ያለ ፈቃዴ ለ ዓባይ ግድብ በማለት ከደመወዜ ቆርጦብኛል  በማለት ክስ የመሰረቱት በሚያስተምሩበት  ትምህርት ቤት ላይ ነው። ትምህርት ቤቱ በ አባይ ግድብ መዋጮ ዙሪያ ከትምህርት ቤቱ መምህራን ...

Read More »