ኢሳት ለማጠናከር በሚኒሶታ ታላቅ የራትና የመዝናኛ ዝግጅት እንደተደገሰ አስተባበሪዎቹ አስታወቁ

ጥር 20 ቀን 2004 ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቭዥንን ለማጠናከር በሚኒሶታ ታላቅ የራትና የመዝናኛ ዝግጅት እንደተደገሰ አስተባበሪዎቹ ለዘ-ሐበሻ ድረ ገጽ በላኩት መግለጫ ላይ አስታወቁ:: በዚህ ዕለት ታዋቂው የሰብዓዊ መብት ተሟጋችና አርቲስት ታማኝ በየነና ድምጻዊ ተሾመ አሰግድ እንደሚገኙ ታውቋል:: “ሚኒሶታውያን ለኢሳት” በሚል መርህ የቴሌቭዥን ጣቢያውን በገንዘብ ለማጠናከር ማርች 18 በኪኤሊ ኢን ሆቴል በሚደረገው በዚሁ የራት ምሽት ላይ ከታማኝ በየነ እና ከድምጻዊ ...

Read More »

በአወልያ መስጊድ የተጀመረው የእስልምና እምነት ተከታዮች ተቀውሞ ዛሬም የአርብ ቀን ስግደትን ተንተርሶ መካሄዱን ዘጋቢያችን ገለጠ

ጥር 19 ቀን 2004 ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ባለፈው ሳምንት በብዙ ሺዎች የሚቆጠሩ ሙስሊሞች በመስጊዱ ግቢና ከመስጊዱ ውጭ በመሆን ስግደት ከሰገዱ በሁዋላ የመብት ጥያቄዎችን በመፈክር ካሰሙ በሁዋላ በተወካዮቻቸው አማካኝነት ከመንግስት ባለስልጣናት ጋር ለመነጋገር ተስማምተው ተለያይተው ነበር። በዛሬው የጁማ ስግደት ካለፈው ሳምንት የበለጠ ህዝብ የተገኘ ሲሆን፣ የተለያዩ የሙስሊሙ ተወካዮች ንግግር አድርገዋል። ኡስታዝ ያሲን ኑሩ በዲናችን ( በሀይማኖታችን) አንደራደርም፣ መሞት ካለብንም እንሞታለን ብለው ለተሰብሳቢው ...

Read More »

መድረክ የከተማን ቦታ በሊዝ ስለመያዝ የወጣውን ዓዋጅ በመቃወም ጋዜጣዊ መግለጫ በጽ/ቤቱ ውስጥ ሰጥቷል

ጥር 19 ቀን 2004 ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ አንድነት መድረክ (መድረክ) የከተማን ቦታ በሊዝ ስለመያዝ የወጣውን ዓዋጅ ቁጥር 721/2004 በመቃወም ዛሬ  አርብ ረፋዱ ላይ ጋዜጣዊ መግለጫ በጽ/ቤቱ ውስጥ ለሀገር ቤትና ለውጭ ጋዜጠኞች ሰጥቷል፡፡ የመድረክ የአመራር አባላት ዶ/ር ሞጋ ፍሪሳ፣ ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ፣ ዶ/ር መረራ ጉዲና፣ አቶ ገብሩ አስራት፣ አቶ ገብሩ ገብረማርያም እና ሌሎችም ከጋዜጠኞች ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች መልስ ሰጥተዋል፡፡ የኢህአዴግ ካድሬዎች ...

Read More »

በእነ ውብሸት ታየና ርእዮት አለሙ ላይ የተላለፈውን ውሳኔ አለማቀፍ የሰብአዊ መብት ድርጅት ተሟጋቾች እያወገዙት ነው

ጥር 19 ቀን 2004 ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ድንበር የለሽ የጋዜጠኞች መብት አስከባሪ ድርጅት በእንግሊዝኛው አጠራር ሪፖርተርስ ዊዝ አውት ቦርደርስ በእነ ውብሸት ታየና ርእዮት አለሙ ላይ የተላለፈው ውሳኔ የኢትዮጵያን ምስል የሚያበላሽ ነው። “የኢትዮጵያን የፍትህ ስርአት መረዳት አይቻልም” ያለው ድርጅቱ ፣በ ህገመንግስቱ የተቀመጡትን መብቶች በግልጽ እንደሚጋፋ በሚነገርለት የጸረ ሽብር አዋጅ ተጠቅሞ ጋዜጠኞችን መቅጣት ተቀባይነት የሌለው ጉዳይ ነው ብሎአል። ርእዮትና ውብሸት ወንጀለኞች ባለመሆናቸው በአስቸኳይ ...

Read More »

ኖርዌይ 400 የሚጠጉ ስደተኞችን ወደ ኢትዮጵያ ለመመለስ ከመንግስት ጋር ስምምነት ማድረጓ ተወቀ

ጥር 19 ቀን 2004 ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የኖርዌይ ጋዜጦች እንደዘገቡት ጉዳያቸው ተቀባይነት ያለገኘ ከ400 በላይ ስደተኞች፣ ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በተደረገው ስምምነት መሰረት ወደ አገራቸው ይመለሳሉ። እስከ መጪው መጋቢት ወር በፈቃደኝነት ወደ አገሩ ለመመለስ የተመዘገበ ስደተኛ ለእያንዳንዱ  40 ሺ ክሮነር ወይም ወደ 6 ሺ ዶላር እንደሚሰጠው  አንድ የፍትህ  ሚኒሰትር ሰራተኛ ተናግረዋል። ባለስልጣኑ ከማርች 15 በሁዋላ እነዚህን ስደተኞች ከአገር በግዴታ ለማስወጣት እንደሚሞክሩን ተናግረዋል። ...

Read More »

የፌደራሉ ከፍተኛው ሶስተኛው ወንጀል ችሎት በእነኤልያስ ክፍሌ መዝገብ በተከሰሱላይ ውሳኔ ሰጠ

ጥር 18 ቀን 2004 ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የኢትዮጵያ ሪቪው ዌብሳይት አዘጋጅ በሆነው ጋዜጠኛ ኤልያስ ክፍሌ ላይ እድሜልክ፣ ሂሩት ክፍሌ 19 አመት፣ ውብሸት ታየ 14 አመትና 33 ሺ ብር ፣ ርእዮት አለሙ 14 አመት እና 36 ሺ ብር እንዲሁም ዘሪሁን ገብረእግዚአብሄርን 17 አመት እስራትና እና 50 ሺ ብር ቅጣት መበየኑን ዳኛ እንዳሻው ገልጠዋል። ውሳኔው አስቀድሞ የተጠበቀ መሆኑን በፍርድ ቤቱ የተገኙት ታዳሚዎች መናገራቸውን ...

Read More »

መድረክ የከተማ ቦታን በሊዝ ስለመያዝ የወጣው አዋጅ ቁጥር 721/2004 በማን አለብኝነት የዜጎችን ንብረት የማፍራት የመሸጥ የመለወጥ እና የመጠቀም መብትን የገፈፈ ነው አለ

ጥር 18 ቀን 2004 ዓ/ም ኢሳት ዜና:-የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ የዜጎች የንብረት ባለቤትነት መብት ይከበር በሚል ርእስ ባወጣው መግለጫ ፣ ለስልጣን ማራዘሚያ ተብሎ የወጣው አዋጅ በህገ መንግስት አንቀጽ ስምንት ንኡስ አንቀጽ 3 የኢትዮጵያ ብሄሮች ፣ ብሄረሰቦችና እና ህዝቦች ሉአላዊነታቸው የሚገለጠው በዚህ ህገመንግስት መሰረት በሚመርጣቸው ተወካዮቻቸው እና በቀጥታ በሚያደርጉት ዲሞክራሲያዊ ተስፎ ይሆናል ቢልም ጉዳዩ የሚመለከተው ህዝብ በነጻነትና በግልጽነት አልተወያየበትም፤ እንዲሁም ...

Read More »

የኢትዮጵያ ህዝብና ዓለማቀፉ ማህበረሰብ ከኢትዮጵያ ጋዜጠኞች ጎን በመቆም ቃል-ኪዳናቸውን እንዲያድሱ የኢት ዮጵያ ነፃ ፕሬስ ጋዜጠኞች ማህበር ጥሪ አቀረበ

ጥር 18 ቀን 2004 ዓ/ም ኢሳት ዜና:-በስደት የሚገኘው ኢነጋማ፦”በጠመንጃ አስገዳጅነት የእውነት እጆች ቢታሰሩም፤ ታሪክና ህዝብ ግን ይፈርዳል” በሚል ርዕስ ባወጣው መግለጫ ፤በኢትዮጵያ ውስጥ ነጻ የሆነ አስተሳሰብ እንዲነግስ፤ በተለይ የኢትዮጵያ ነጻ ፕሬስ ጋዜጠኞች ታላቁን ሚና መጫዎታቸውን እንዲሁም፤ ሃሳብን በነጻነት መግለጽ ፤ተፈጥሯዊና  በኢትዮጵያዊያን የትግል ውጤት የተገኘ እንጂ፤ የኢህአዴግ ችሮታና ስጦታ እንዳልሆነ ድምጻቸውን ከፍ አድርገው ማሰማታቸውን አስታውሷል  አልፎ ተርፎም  ስልጣን ከጠመንጃ ውስጥ በሚወጣ ...

Read More »

ከኢትዮጵያውያን ጋር በጋራ ለአንዲት ኢትዮጵያ ለመታገል የወሰነው የኦሮሞ ነፃነት ግንባርና የግንቦት 7 ንቅናቄ በሚኒሶታ ታላቅ ህዝባዊ ስብሰባ ያደርጋሉ

  ጥር 18 ቀን 2004 ዓ/ም ኢሳት ዜና:-ከኢትዮጵያውያን ጋር በጋራ ለ አንዲት ኢትዮጵያ ለመታገል የወሰነው የ ኦሮሞ ነፃነት ግንባርና የግንቦት 7 ለፍትህ፣ለነፃነትና ለዲሞክራሲ ንቅናቄ በመጪው ፌብሩዋሪ ወር በሚኒሶታ ታላቅ ህዝባዊ ስብሰባ እንደሚያደርጉ ዘ-ሀበሻ ዘገበ። በኦነግ የሰሜን አሜሪካ አስተባባሪና የህግ አማካሪ የሆኑትን ዶክተር ነሩ ደደፎን በመጥቀስ ዘ-ሀበሻ እንደዘ ገበው  በመቺው ወር አጋማሽ በሁለቱ ድርጅቶች መካከል የሚካሄደው ታላቅ ስብሰባ ሁሉንም ኢትዮጵያውያን ያካተተ ...

Read More »

የፌዴራል ዐቃቤ- ህግ በእነ አንዱአለም አራጌና እስክንድር ነጋ ላይ ብይን ሰጠ

ጥር 16ቀን 2004 ዓ/ም ኢሳት ዜና:-በህጋዊ ፓርቲ ጥላ ስር ተከልለው የመንግሥት ባለስልጣናትን ለመግደል፣ መሠረተ ልማቶችን ለማውደም እና ከአሸባሪ ቡድኖች ጋር አንድ ላይ በማበር ሕገመንግሥቱንና ሕገመንግሥታዊውን መንግስት ለመገልበጥ በሀገር ውስጥና በውጭ አገራት አሲረው ተንቀሳቅሰዋል ሲል የከሰሳቸው 24 የፖለቲካ ፓርቲ የአመራር አባላት፣ ጋዜጠኞች እና ነፃ አሳቢ ዜጎች ላይ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ሦስተኛ ወንጀል ችሎት ትናንት የጥፋተኝነት ብይን ሰጥቷል:: ዘጋቢያችን እንደገለጠው ...

Read More »