511 የሚሆኑ ከቤኒሻንጉል ጉምዝ ና ከኦሮሚያ ክልል የተፈናቀሉ የአማራ ብሄር ተወላጆች እስካሁን መፍትሄ አላገኙም ፡፡

511 የሚሆኑ ከቤኒሻንጉል ጉምዝ ና ከኦሮሚያ ክልል የተፈናቀሉ የአማራ ብሄር ተወላጆች እስካሁን መፍትሄ አላገኙም ፡፡
( ኢሳት ዜና ሃምሌ 4 ቀን 2010 ዓ/ም ) ተፈናቃዮቹ የአማራ ብሄራዊ ክልል ምክር ቤት ስብሰባን ምክንያት በማድረግ ወደ ስብሰባ ቦታው በመሄድ ችግራቸው እንዲታይላቸው የጠየቁ ሲሆን፣ የክልሉ አመራሮች ለአጭር ጊዜ አግኝተው አነጋግረዋቸዋል። ባለስልጣናቱ እስከ መጪው ቅዳሜ ስብሰባ ላይ መሆናቸውንና እሁድ አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ተፈናቃዮችን እንደሚያናግሩዋቸው ገልጸውላቸው ተፈናቃዮቹን አሰናብተዋቸዋል።