የወልቂጤ ከተማ ነዋሪዎች የተለያዩ ጥያቄዎችን ለጠ/ሚኒስትሩ አቀረቡ

የወልቂጤ ከተማ ነዋሪዎች የተለያዩ ጥያቄዎችን ለጠ/ሚኒስትሩ አቀረቡ
(ኢሳት ዜና ሰኔ 13 ቀን 2010 ዓ/ም) ዶ/ር አብይ አህመድ በተገኙበት ስብሰባ በርካታ ጥያቄዎች ተነስተዋል። “የጉራጌ ህዝብ የክልል ጥያቄ መልስ ያግኝ፣ የጉራጌ ምሁራንን ማግለል ለምን ተፈለገ? ጉራጌን ከንግድ አለም ለማስወጣት አሻጥር ሲፈጸምበት ደኢህዴን የት ነበር? በቀቢናና ጉራጌ ብሄረሰቦች መካካል ግጭት የቀሰቀሱት ለፍርድ ይቅረቡ” የሚሉ ጥያቄዎች ቀርበዋል።
ዶ/ር አብይ ሰሞኑን በክልሉ ግጭት የቀሰቀሱ አካላት በራሳቸው ጊዜ ስልጣን ይለቃሉ ብለው እንደሚያምኑና ስልጣንም እንዲለቁ ጥሪ አቅርበዋል።