የመንግስታቱ ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ገተርስ ኢትዮጵያ እና ኤርትራ በመካከላቸው የነበረውን ውዝግብ ለመፍታት እና ወደ ሰላም ለመምጣት መስማማታቸውን አደነቁ።

የመንግስታቱ ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ገተርስ ኢትዮጵያ እና ኤርትራ በመካከላቸው የነበረውን ውዝግብ ለመፍታት እና ወደ ሰላም ለመምጣት መስማማታቸውን አደነቁ።
(ኢሳት ዜና ሰኔ 14 ቀን 2010 ዓ/ም)ዋና ጸሀፊው የሁለቱ ሀገራት መሪዎች በመካከላቸውና በአጎራባች ሀገራት ጭምር ዘላቂ ሰላም ለማምጣት የሚያስችል ስምምነት ለማምጣት እያደረጉ ያለውን ጥረትም አወድሰዋል።.
ከዋና ጸሀፊው ቃል አቀባይ ጽህፈት ቤት የወጣው መግለጫ እንደሚለው፣ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ወደ ሰላማዊ መንገድ መመለሱ፣ በአጠቃላይ በአፍሪካ ቀንድ ሀገራት ሰላም ለማስፈን አስተዋዖው ከፍ ያለ ነው።
ሀገራቱ ሰላም ለመፍጠር በሚከተሏቸው ሂደቶች ተመድ አስፈላጊ የሆኑ ድጋፎችን ሁሉ ላማድረግ ዝግጁ መሆኑንም አንቶኒዮ ገተርስ አስታውቀዋል።.