ኢዜማ የፓርቲውን መሪዎች በመምረጥ ጉባዔውን አጠናቀቀ

(ኢሳት ዲሲ–ግንቦት 2/2011) የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ኢዜማ የፓርቲውን መሪዎች በመምረጥ የመስራች ጉባዔውን አጠናቀቀ።

የሰባት ፓርቲዎች ውህድ በመሆን የተመሰረተው ኢዜማ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋን የፓርቲው መሪ፣ አቶ አንዱዓለም አራጌን በምክትልነት መርጧል።

አቶ የሺዋስ አሰፋን የፓርቲው ሊቀመንበር፣ ዶክተር ከበደ ጫኔን ደግሞ በምክትል ሊቀመንበርነት መምረጡ ታውቋል።

ከ300 በላይ ወረዳዎች ተወካዮቻቸውን በመላክ በአዲስ አበባ ለሁለት ቀናት ጉባዔውን ያካሄደው የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ ዜግነት ላይ መሰረት ያደረገ የፖለቲካ መስመር እንደሚከተልም ይፋ አድርጓል።