ታዋቂው የኢሳት ጋዜጠኛ ንጉሴ ጋማ አረፈ

ግንቦት ፲፯ (አስራ ሰባት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም

ኢሳት ዜና:- ጋዜጠኛ ንጉሴ ጋማ በኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥን በጋዜጠኝነት ያገለግሉ ነበሩ:: በደረሰባቸው ድንገተኛ ህመም ለጥቂት ጊዜ  በህክምና ሲረዱ ቆይተው ግንቦት 16 ቀን 2004 ዓ/ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል::

ጋዜጠኛ ንጉሴ ጋማ ባለትዳርና  የ4 ልጆ ች አባት እንዲሁም የሁለት ልጆች አያት ነበሩ::

በጋዜጠኛ ንጉሤ ጋማ የህይወት ታሪክ ዙሪያ የተዘጋጀ ዘጋቢ ፊልም በቅርቡ ይዘን እንቀርባለን።

በዚህ አጋጣሚ ለጋዜጠኛ ንጉሴ ጋማ ቤተሰቦች፣ዘመድ አዝማዶች ጓዸኞች፣ የሥራ ባልደረቦች እና ሀሳብን በነፃነት የመግለጽ መብት በአገራችን እንዲረጋገጥ ያለመታከት በጽናት ሢሰራ የቆየው የነፃነቱ ዘብ ንጉሴ ጋማ በማረፉ ሀዘን ለተሰማችሁ  በሙሉ፤ የኢሳት ዝግጅት ክፍል መጽናናት እንዲሆንላችሁ ልባዊ ምኞቱን ይገልፃል።

___________________________________________________________________________________________________________________________________________________

ESAT is the first independent Ethiopian satellite service tasked to produce accurate and balanced news and information, as well as other entertainment, sports and cultural programming created for and by Ethiopians.

ESAT is committed to the highest standards of broadcast journalism and programming and will strive to provide an outlet of expression to all segments of the diverse Ethiopian community worldwide