ቦሌ መንገድ የንግድ ማእከልነቱ እያከተመ ነው ተባለ

የካቲት 24 ቀን 2004 ዓ/ም

ኢሳት ዜና:-በቅርቡ በቦሌ መስመር የተጀመረው የመንገድ ግንባታ የመኪና ማቆሚያ ወይም ፓርኪንግ የሚተው ባለመሆኑ፣ የቦሌ የንግድ ማእከልነት እያበቃ መምጣቱን ነዋሪዎች ተናግረዋል።

የኢሳት ዘጋቢ ነዋሪዎቹን አነጋግሮ እንደዘገበው ከአብዮት አደባባይ እስከ ቦሌ አየር ማረፊያ በሚወስደው መንገድ ላይ የመኪና ማቆሚያ ቦታ አልተተወም። በዚህም የተነሳ የቦሌ የንግድ ማእከልነት የሚቀዘቅዝ በመሆኑ፣ በአካባቢው የንግድ ድርጅቶችን ተከራይተው ሲሰሩ የነበሩ ሰዎች እየለቀቁ ነው። በርካታ ደርጅቶች መዘጋታቸውንም ዘገባያችን ገልጧል።

የቻይና መንግስት የቦሌን መንገድ መልሶ ለመገንባት የገንዘብ ድጋፍ ማድረጉ ይታወቃል።

___________________________________________________________________________________________________________________________________________________________________________

ESAT is the first independent Ethiopian satellite service tasked to produce accurate and balanced news and information, as well as other entertainment, sports and cultural programming created for and by Ethiopians.

ESAT is committed to the highest standards of broadcast journalism and programming and will strive to provide an outlet of expression to all segments of the diverse Ethiopian community worldwide