በፓሪስ ከአራተኛ ፎቅ ቁልቁል ሊወድቅ የነበረን የአራት ዓመት ህጻን ልጅ የታደገው ማላዊ ስደተኛ፣ የፈረንሳይ ዜግነት ተሰጠው።

በፓሪስ ከአራተኛ ፎቅ ቁልቁል ሊወድቅ የነበረን የአራት ዓመት ህጻን ልጅ የታደገው ማላዊ ስደተኛ፣ የፈረንሳይ ዜግነት ተሰጠው።
(ኢሳት ዜና ግንቦት 20 ቀን 2010 ዓ/ም) ማሞዱ ጋሴማ የተባለው ይህ ወጣት ማላዊ ከፎቅ ላይ ቁልቁል ሊከሰከስ የነበረን ህጻን በደረቱ ተስቦ በመውጣት የመታደጉ ዜና ከተሰማ በኋላ፣በፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮንና በመላው ፈረንሳውያን ዘንድ ታላቅ አክብሮትና ምስጋና ተችሮታል። በኤሊሴ በሚገኘው ቤተሰምንግስ ከፕሬዚዳንት ማክሮን ጋር ከተገናኘም በኋላ የፈረንሳይ ዜግነት ተሰጥቶታል።
ፕሬዚዳንቱ ከዚህም ባሻገር ለማሞዱ-ሜዳሊያ ያበረከቱለት ሲሆን፣ በሀገሪቱ እሳት አደጋ ብርጌድ ውስጥ እንዲሠራ ሀሳብ አቅርበውለታል።የማሊው ወጣት ማሞዱ፣ ከአስከፊና አደገኛ ጉዞ በኋላ ባለፈው ዓመት ሜዲትራኒያን ባህርን አቆራርጦ በጀልባ አውሮፓ መግባቱን ገልጿል። ፈረንሳውያኑ-በደረቱ እየተሳበ እስከ አራተኛው ፎቅ ድረስ በመውጣት የአራት ዓመቱን ህጻን የታደገውን ማሞዱን፣”ሸረሪቱ” የሚል ቅጽል ስም ሰጥተውታል።