በጋሞጎፋ ዞን የሚገኙ ነዋሪዎች በአካባቢያቸው ከፍተኛ ግጭት ሊፈጠር ይችላል ሲሉ ስጋታቸውን ገለጡ

ግንቦት ፲፫ (አስራ ሦስት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም

ኢሳት ዜና:-የመንግስት  ባለስልጣናት በፈጠሩት ችግር ለዘመናት  አብረው የኖሩ የአካባቢው ነዋሪዎች እርስ በርስ ለመጋጨት ተፋጠዋል ሲሉ የአካባቢው ነዋሪዎች ለኢሳት ገልጠዋል።

የደምባ ጎፋ ወራዳ አስተዳዳሪና ምክትል አስተዳዳሪ ሰሞኑን ወደ ዛንዳ  ቀበሌ በመሄድ ግጭት ለመፍጠር መሞከራቸውን አንድ የአካባቢው ተዋቂ አዛውንት ተናግረዋል::

አዛውንቱ በአካባቢያቸው ያለው ችግር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱንም ይገልጣሉ ። እርሳቸው እንደሚሉት ከስምንተኛ ክፍል ጀምሮ የሚማሩ ተማሪዎች የኢህአዴግ አባል ካልሆኑ ለመማር በማይችሉበት ደረጃ ላይ ደርሰዋል::

___________________________________________________________________________________________________________________________________________________

ESAT is the first independent Ethiopian satellite service tasked to produce accurate and balanced news and information, as well as other entertainment, sports and cultural programming created for and by Ethiopians.

ESAT is committed to the highest standards of broadcast journalism and programming and will strive to provide an outlet of expression to all segments of the diverse Ethiopian community worldwide