በኦቢኤን ለሚሰሩ ጋዜጠኞች በአዲስ አበባ ከተሰሩ ኮንዶሚኒየም ቤቶች እንዲሰጣቸው ተደረገ

(ኢሳት ዲሲ–መጋቢት 10/2011)በኦሮሚያ ብሮድካስቲንግ ኔትወርክ /ኦቢኤን/ ለሚሰሩ ከ40 በላይ ጋዜጠኞች በአዲስ አበባ ከተሰሩ ኮንዶሚኒየም ቤቶች በከተማዋ ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ ትዕዛዝ ያለእጣ በነጻ እንዲሰጣቸው ተደረገ ።

ለኢሳት በደረሰው መረጃ መሰረት የስም ዝርዝራቸው የተካተተበት የኦቢኤን ጋዜጠኞች ኮንዲሚኒየም ቤት እንዲሰጣቸው ለከተማዋ ከንቲባ ትብብር ይደረግ ብሎ የጻፈው የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ፕሬዝዳንት ጽህፈት ቤት ነው።

ጋዜጠኞቹ ስም ዝርዝራቸው ሲተላለፍ በኦቢኤን ውስጥ በከፍተኛ አመራር ላይ ያሉ ሹመኞች በማስመሰል መሆኑንም ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።