በአፋር ሰመራ ህዝባዊ ተቃውሞ ተቀሰቀሰ

(ኢሳት ዲሲ–ግንቦት 21/2010)በአፋር ክልል ሰመራ ህዝባዊ ተቃውሞ ተደረገ።

የሰመራ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎችም በአፋር ያለው የመልካም አስተዳደር እጦት በመባባሱ ተቃውሞ በማድረግ ላይ መሆናቸውን የደረሰን መረጃ አመልክቷል።

እስራትና ማፈናቀል በአፋሮች ላይ እየተጠናከረ መሆኑን በመጥቀስም ህዝቡ ተቃውሞውን ሲያሰማ መዋሉን ለማወቅ ተችሏል።

ከሁለት ሳምንት በፊት በአፋር ክልል ሰመራና ሌሎች ከተሞች ህዝባዊ የተቃውሞ ጥሪ የሚያደርግ በራሪ ወረቀት መበተኑን ተከትሎ በሌሎችም አካባቢዎች ተመሳሳይ ተቃውሞ ሊኖር እንደሚችል ነው የኢሳት የመረጃ ምንጮች የገለጹት።