በነጭ አክራሪዎች የተጠራው ሰላማዊ ሰልፍ ተቃውሞ ገጠመው

(ኢሳት ዲሲ–ነሐሴ 7/2010) በዋሽንግተን ዲሲ ትላንት በነጭ አክራሪዎች የተጠራው ሰላማዊ ሰልፍ ከፍተኛ ተቃውሞ ገጠመው።

ከ30 የማይበልጡ ስብስቦችን የያዘው የነጭ አክራሪ ቡድን በጠራውን ሰልፍ ተከትሎ የተለያዩ የሰብአዊ መብት ተከራካሪዎች ለተቃውሞ አደባባይ ወተዋል።

ባለፈው አመት በተመሳሳይ በቻርለስ ቬት ቨርጂኒያ በተጠራ ሰላማዊ ሰልፍ ላይ በተነሳ ግጭት የአንዲት ሴት ህይወት ማለፉ የሚታወስ ነው።

የናዚ ደጋፊዎችና ዘረኞች በከተማችን ዲሲ ቦታ የላቸውም ሲሉ ተቃውሟቸውን ያሰሙት ሰልፈኞቹ በሁለቱ ወገኖች መካከል የሃይለ ቃል መሰናዘር ቢኖርም ከሞላጎደል በሰላማዊ ሁኔታ መጠናቀቁን ሲ ኤን ኤን በዘገባው አስፍሯል።