ዶክተር ደብረጺዮን ገብረ ሚካኤልን የወሲብ ቅሌት ይፋ ሆነ

(ኢሳት ዲሲ–ጥር 3/2010)

የሕወሃት ሊቀመንበር ዶክተር ደብረጺዮን ገብረ ሚካኤልን የወሲብ ቅሌት የሚያሳይ ማስረጃ ይፋ ሆነ።

ዶክተር ደብረጺዮን በወሲብ ጉዳይ ላይ የኢሜልና የኢንተርኔት ግንኙነትን የሚያጋልጥ መረጃ ተሰብሮ ወጥቷል።

በወጣው መረጃ ላይ ዶክተር ደብረጺዮን ዘወትር የሚጎበኟቸውን የወሲብ ድረገጾች፣ከዝሙት አዳሪዎች ጋር ያደረጓቸውን ግንኙነቶችና ሌሎች ቅሌቶች ይፋ ሆነዋል።

የትግራይ ክልልን እንዲመሩ ትላንት የተሰየሙት ዶክተር ደብረጺዮን ገብረሚካኤል የኤሌክትሮኒክስ መልዕክት ሳጥናቸው ተሰብሮ ይፋ የሆነው መረጃ የቴክኖሎጂ እውቀታቸውን ጥያቄ ውስጥ አስገብቶታል።

ከፍተኛ የስነ ምግባር ጉድለት ያለባቸው መሆኑንም አጋልጧል።

የተበተኑትን መረጃዎች ትክክለኛነት በባለሙያዎች አስጠንቶ በማረጋገጥና ተጨማሪ መረጃዎችን በማካተት ሪፖርቱን በ15 ገጽ ያጠናቀረው ጋዜጠኛ አበበ ገላው ዶክተር ደብረጺዮን ከ10 በሚበልጡ የአላማችን ከተሞች የነበራቸውን ቆይታ ፈትሿል።

ገብረሚካኤል መለስ በተባሉ የትግራይ ክልል የኮሚኒኬስን ጉዳዮች ሃላፊ ማህበራዊ ገጽ ላይ በይፋ ከወጣ በኋላ በሕዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ ደጋፊዎች ዘንድ ከፍተኛ ጫጫታ የፈጠረው መረጃ ወዲያውኑ እንዲሰረዝ ተደርጓል።

ሆኖም መረጃው አስቀድሞ በመበተኑ በተለያዩ ወገኖች እጅ መግባት ችሏል።

በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የኮሚኒኬሽንና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስትር እንዲሁም የህወሃት ሊቀመንበር የሆኑት ዶክተር ደብረጺዮን ገብረሚካኤል የኤሌክትሮኒክስ መልዕክት ሳጥናቸው ጋር በተያያዘ መበርበሪያ/ብራውዘር/ የሚያደርጉት የድረ ገጽ አሰሳም የቴክኖሎጂ እውቀታቸውንም ጥያቄ ውስጥ አስገብቶታል።

በተለያዩ የአለም ክፍሎች በሚያደርጉት ጉዞ የዝሙት አዳሪዎችን አድራሻ በቋሚነት የማሰስ ተግባራቸውም ይበልጥ ትኩረትን የሳበ ሆኖ ተገኝቷል።

እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር ሚያዚያ 24/2012 በካይሮ በተካሄደው የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ስብሰባ ላይ ተገኝተው ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ድርቅን መሰል አደጋዎችን ለመከላከል ያለውን ሚና የዘረዘሩ ቢሆንም በዕለቱ ኮምፒዩተራቸውን ከፍተው ከመረጃ ባህር ሲበረብሩ የነበሩት በካይሮ የሚገኙ በዝሙት የሚተዳደሩ ሴቶችን የሚያገናኙ ድረገጾችን እንደነበር ከተሰበረው የመልዕክት ሳጥናቸው የተገኘው መረጃ አጋልጧል።

በቅርቡ የዛሬ ስድስት ወር እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር መስከረም 26/2017 አለም አቀፉ የቴሌኮሚኒኬሽን ዩኒየን ባዘጋጀውና በደቡብ ኮሪያ ቡሳን በተካሄደው ስብሰባ ላይ የተገኙት ዶክተር ደብረጺዮን ገብረሚካኤል በቆይታቸው በኢንተርኔት ሲበረብሩት የነበሩት በቡሳንና በርዕሰ መዲናዋ ሴኡል የሚገኙ በዝሙት የሚተዳደሩ ሴቶችን የሚያገናኙ ድረገጾችን እንደነበርም በሰነዱ ላይ በዝርዝር ተመልክቷል።

ለመንግስታዊ ስራና ሃላፊነት በተለያዩ የአለም ክፍሎች ሲጓዙ ከሄዱበት መንግስታዊ ሃላፊነት ይልቅ የየከተሞቹን የሴተኛ አዳሪዎችን አድራሻ ሲበረብሩ የሚያጋልጠው ሰነድ በቀንና በሰአት በዝርዝር ተቀምጧል።

ከግብጽ ካይሮ እንዲሁም ከደቡብ ኮሪያ ቡሳን ባሻገር በካሜሮን ያውንዴ፣በታይላንድ ባንኮክ፣በጃፓን ሄሮሽማና ቶኪዮ፣በሕንድ ሙምባይ፣በዩናይትድ አረብ ኢምሬት ዱባይ፣በአሜሪካ ላስቬጋስ ከተሞች ለመንግስታዊ ስራ በተጓዙበት ወቅት የዝሙት አደር ሴቶችን አድራሻ ሲበረብሩና አገናኝ ድረገጾችን ሲያስሱ እንደነበርም ይፋ ሆኗል።