በአርበኞች ግንቦት7 የተከሰሱት በፍርድ ቤት ውስጥ መፈክር አሰሙ

በአርበኞች ግንቦት7 የተከሰሱት በፍርድ ቤት ውስጥ መፈክር አሰሙ
(ኢሳት ዜና ግንቦት 06 ቀን 2010 ዓ/ም) በእነ ሚፍታህ ሸህ ሱሩር ክስ መዝገብ በአርበኞች ግንቦት 7 ተከሰው ልደታ ፍርድ ቤት የቀረቡ በቁጥር ከ40 በላይ የሚሆኑ ተከሳሾች በፍርድ ቤቱ ግቢ ውስጥ መፈክር አሰምተዋል። የህሊና እስረኞች “ የነፃነት ታጋዮች እንጅ አሸባሪዎች አይደለንም፣ እንደ ማዕከላዊ እስር ቤት ቂሊንጦም ይዘጋ፣ ግፍ ይብቃ፣ ስቃይ ይብቃ” ብለዋል።
በእነ ሚፍታህ ሸህ ሱሩር ክስ መዝገብ ከተከሰሱት 77 ተከሳሾች መካከል ግማሾቹ አምነው በመከራከራቸው ከ15 እስከ 17 አመት ተፈርዶባቸዋል።