ታህሳስ 07 ቀን 2004 ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-ኢትዮጵያኑ እሁድ ዲሰምበር 18 በአምስተርዳም ከተማ በሚያካሂዱት የሻማ ማብራት ስነስርአት ፣ የኔሰው ገብሬ ለኢትዮጵያ ህዝብ የከፈለውን መስዋትነት በመዘከር፣ በውጭ የሚገኘው ኢትዮጵያዊ በአገሩ ጉዳይ ላይ ስለሚኖረው ሀላፊነት ምክክር እንደሚደረግ የአምስተርዳም የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ሊቀመንበር አቶ ወንድወሰን ገብረህይወት ለኢሳት ገልጠዋል።
በአሪቢሞንድ ስትራት ከሰአት በሁዋላ 5 ፒኤም በሚደረገው ስነስርአት ላይ የተለያዩ የፖለቲካ ድርጅት ተወካዮች፣ የመገናኛ ብዙሀን ወኪሎችና የሲቪክ ማህበረሰብ አባላት ንግግር ያደርጋሉ።
በሆላንድ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን በስፍራው ተገኝተው የኔሰው ገብሬን እንዲዘክሩ ሊቀመንበሩ ጥሪ አቅርበዋል።
ESAT Amharic ESAT Amharic News