ለታሰሩት የሙስሊም መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴዎችና ጋዜጠኞች ፍርድ ቤት ረዥም ቀጠሮ ሰጠ።

ነሃሴ ፴(ሠላሳ)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-መንግስት በሽብርተኝነት በከሰሳቸውና ጉዳያቸው በመታየት ላይ ባለው የሙስሊም መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴዎች ላይ በፍርድ ቤት ረዥም ቀጠሮ መሰጠቱ አነጋጋሪ ሆነ። የኢሳት ዘጋቢ ከአዲስ አበባ እንዳጠናቀረው መረጃ  ታሳሪዎቹ ብይን ለመስማት  ከ3 ወር በላይ መጠበቅ አለባቸው። በሐምሌ ወር  2004 ኣመተ ምህረት የፈጠራ ሽብርተኝነት ክስ ተመስርቶባቸው ላለፉት ሀለት ኣመታት በእስር ላይ በሚገኙት የሙስሊሞች የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት፣ የሃይማኖት ...

Read More »

ኬንያ ከአለማቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት አባልነት ለመልቀቅ ወሰነች

ነሃሴ ፴(ሠላሳ)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኬንያ ከአምስት አመታት በፊት የተደረገውን ምርጫ ተከትሎ በሞቱ ከ1ሺ በላይ ዜጎች የአሁኑ አገሪቱ መሪ ኡሁሩ ኬንያታና ምክትላቸው ዊሊያም ሩቶ በሰው ልጆች ላይ በተፈጸመ ወንጀል በአለማቀፉ ፍርድ ቤት ተጠያቂዎች ሆነዋል። ሁለቱም መሪዎች ፍርድ ቤት እንደሚቀርቡ በሚታወቅበት ሰአት አገራቸውን ከፍርድ ቤቱ አባልነት በማስወጣት ራሳቸውን ከጠጠያቂነት ለማዳን የወሰዱት እርምጃ የአገሪቱን ተቃዋሚዎች አስቆጥቷል። ሁለቱ መሪዎች ከፍርድ ቤቱ ጋር ...

Read More »

ፕሬዚዳንት ኦባማ በሶሪያ ላይ ለሚወስዱት ወታደራዊ ጥቃት ድጋፍ ለማሰባሰብ እየሞከሩ ነው

ነሃሴ ፳፱(ሃያ ዘጠኝ)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የአገራቸውን ወሳኝ ፖለቲከኞች ድጋፍ ያገኙት ፕሬዚዳንት ኦባማ፣ አለማቀፍ ድጋፍ ለማግኘት የሚያደርጉትን ዘመቻ ዛሬ በስዊድን ጀምረዋል። አለም ያስቀመጠው ቀይ መስመር አለ፣ያም መስመር ” የኬሚካል የጦር መሳሪያዎችን መጠቀም አይቻልም” የሚል ነው፤ አለም ለዚህ ውሳኔው በጋራ ሊቆም ይገባል ብለዋል ፕሬዚዳንቱ። ከአውሮፓ አገራት መካከል  እስካሁን ድረስ ለአሜሪካ እርምጃ ድጋፏን የገለጸችው ፈረንሳይ ብቻ ናት። ይህ በእንዲህ እንዳለ የሩሲያው ...

Read More »

በበባህርዳር አንድ የፖሊስ ኢንስፔክተር ተገደለ

ነሃሴ ፳፱(ሃያ ዘጠኝ)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ወረዳ ሁለት እየተባለ ለሚጠራው አካባቢ ሀላፊ የነበረው ኢንስፔክተር ምትኩ ዛሬ ጠዋት በመኪና ተገጭቶ ሞቷል። ድርጊቱን የፈጸሙት ሰዎች እስካሁን ያልተያዙ ሲሆን ፣ ጉዳዩን በመመርመር ላይ የሚገኙት ዋና ኢንስፔተር ውበቱ ለኢሳት እንደገለጹት ድርጊቱ በምን ምክንያት እንደተፈጸመ ለማወቅ ምርመራ እየተካሄደ ነው ብለዋል። በግለሰቡ የተከፉ ሰዎች ሆን ብለው ገድለውት አምልጠዋል ይባላል በሚል ለቀረበላቸው ጥያቄ፣ ኢንስፔክተሩ እስካሁን ያለን ...

Read More »

የአዲስ አባባ ዩኒቨርሲቲ የማስፋፊያ ፕሮጀክት ገጠመው፡፡

ነሃሴ ፳፱(ሃያ ዘጠኝ)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የዩኒቨርስቲው የማስፋፊያ ፕሮጀክት በኢትዮጵያ መንግሥት በተመደበ 859 ሚሊዮን 514 ሺ 332 ብር ከ42 ሳንቲም በ‹‹CDS consultancy›› ድርጅት አማካሪነት እና በሌሎች 15 ተቋራጮች ከ2001 ዓ/ም እስከ 2003 ዓ/ም ባሉት ጊዚያት  ተጀምሮ በመካሄድ ላይ ነው። አጠቃላይ ፕሮጀክቶቹን ለማጠናቀቅ የተያዘው የጊዜ ሠሌዳ ዝቅተኛው 2 ወር ከ15 ቀናት ከፍተኛው ደግሞ 49 ወራት ነው፡፡ በማስፋፊያ ፕሮጀክቱ እየተከናወኑ ከሚገኙ ...

Read More »

የመንግስት ኮምኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ሚ/ር በትላንትናው ዕለት በሒልተን ሆቴል ድንገት በጠራው የእራት ግብዣ አዲሱ ሚኒስትርን ከጋዜጠኞችና የኮምኒኬሽን ባለሙያዎች ጋር አስተዋወቀ፡፡

ነሃሴ ፳፱(ሃያ ዘጠኝ)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በቅርቡ አቶ በረከት ስምኦንን በመተካት በሚኒስትርነት ወደ ጽ/ቤቱ የመጡት አቶ ሬድዋን ሁሴንን ያስተዋወቁት አቶ ሽመልስ ከማል ሲሆኑ ሰውየው ከሚዲያ ጋር ባላቸው ቅርበት፣በአንደበተ ርዕቱነታቸው፣በፖለቲካ ዕውቀታቸው የላቁ መሆናቸውን ለጋዜጠኞች በመንገር አስተዋውቀዋቸዋል፡፡ ከሳምንት በፊት ከዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን ዳይሬክተርነት ተነስተው በመንግስት ኮምኒኬሽን ጽ/ቤት በሚኒስትር ዴኤታነት ማዕረግ የተሾሙት አቶ እውነቱ ደበላም በተመሳሳይ መንገድ ተዋውቀዋል፡፡ አቶ እውነቱ ወደ ...

Read More »

በአዳማ/ ናዝሬት የአንድነት ፓርቲ አባላት መዋከባቸው ታውቀ

ነሃሴ ፳፱(ሃያ ዘጠኝ)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አንድነት ፓርቲ በመጪው እሁድ በከተማዋ ለሚያደርገው የተቃውሞ ሰልፍ የቅስቀሳ ወረቆቶችን ሲበትኑ የነበሩ ወጣቶች ለአጭር ጊዜ ተይዘው ተፈተዋል። ፓርቲው ሰለማዊ ሰልፍ እንዲአካሂደ ፈቃድ ከተሰጠው በሁዋላ፣ ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ እንጅ ወረቀት የመበተን ፈቃድ አልተሰጣችሁም በሚል ሰበብ ወጣቶቹ እንዲታሰሩ መደረጉ ታውቋል። ኢሳት ከኢህአዴግ የአዳማ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ባገኘው አስተማማኝ መረጃ ፣ ፖሊሶችና የደህንነት ሀይሎች ፓርቲው የሚያደርገውን ...

Read More »

ላለፉት 2 አመታት ስርአቱን በሀይል ለመፈታተን ከሞከሩት ሁሉ የሀይማኖት እንቅስቃሴዎች ዋነኞቹ እንደነበሩ ኢህአዴግ አስታወቀ

ነሃሴ ፳፰(ሃያ ስምንት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ፓርቲው አዲስ ራእይ በሚባለው ልሳኑ ” ፣ በሀይማኖት ሽፋን የሚካሄዱ የፖለቲካ እንቅስቃሴዎች እየተዳከሙና እየተጋለጡ መሄዳቸው ባይቀርም ባለፉት ሁለት አመታት ልማታዊና ዲሞክራሲያዊ ስርአቱን በሐይል ለመፈታተን ከመከሩት የሁከት ሀይሎች ዋነኞቹ ነበሩ ማለት ይቻላል” ብሎአል። ኢህአዴግ ከአክራሪዎች ጎን በመቆም አመጽ ለማነሳሳት ሞክረዋል ካላቸው ድርጅቶች መካከል ድምጻችን ይሰማ፣ ግንቦት 7 አሜሪካ ድምጽ ሬዲዮና ቢላል ሬዲዮ በዋናነት ተጠቅሰዋል። ...

Read More »

የኢትዮጵያ መንግሥት በሰማያዊ ፓርቲ ላይ ጥቃት አላደረስኩም ሲል መካዱን ቢቢሲ ዘገበ።

ነሃሴ ፳፰(ሃያ ስምንት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ባለፈው እሁድ በአዲስ አበባ ሰማያዊ ፓርቲ ሊያደርገው የነበረውን የተቃውሞ ሰልፍ በሀይል የጨፈለቀው የ ኢህአዴግ መንግስት፤ በርካታ የፓርቲውን አባላት እንዳሰረ ፣ እንደደበደበና እና የጽህፈት ቤቱን ንብረት እንደመዘበረ ፓርቲው መግለጹን ቢቢሲ በትናንት ዘገባው አመልክቷል። የፓርቲውን  ሊቀመንበር ይልቃል ጌትነትን በመጥቀስ የዜና አውታሩ እንደዘገበው፤ እሁድ ሊካሄድ ለነበረው ሰላማዊ ሰልፍ በፓር ቲያቸው የተዘጋጁ የድምጽ መሣሪያዎች በታጣቂዎች ተወስደዋል፤ ሰልፉም ...

Read More »

ለኪነ ጥበብ ባለሙያዎችና ጋዜጠኞች በድጋሜ ታላቅ ግብዣ ተዘጋጀ

ነሃሴ ፳፰(ሃያ ስምንት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ከአራት ሚሊየን ብር በላይ ወጪ የወጣበትና በኢፌዴሪ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አስተባባሪነት የኪነጥበባት ባለሙያዎች፣ ምሁራንና የሚዲያ ባለሙያዎች ቡድን የተሳተፉበት የጉብኝት ፕሮግራም ከግንቦት 24 እስከ ሰኔ 4/2005 ዓ/ም በኢትዮጵያ ሶማሊ ክልል መካሄዱ የሚታወስ ሲሆን ይህንን መነቃቃትና የገጽታ ግንባታ አጠናክሮ ለመቀጠል ያስችላል የተባለ ታላቅ ድግስ ጳጉሜ 3 ቀን 2005 በሸራተን ሆቴል ተዘጋጀ፡፡ አርቲስቶችና ጋዜጠኞች የተሰባሰቡበት ...

Read More »