በቦረና እና በጉጂ ጎሳዎች መካከል የተፈጠረው ግጭት ወደ ሌሎች አካባቢዎችም እየተዛመተ ነው

ሚያዚያ ፰ (ስምንት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከትናንት በስቲያ በቦረና ዞን መልካ ሶዳ ወረዳ ሃሎ ቀበሌ 2 የጉጂ ተወላጆች ተገድለው መገኘታቸውን ተከትሎ የመልካ ሶዳ ሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች ተቃውሞ አሰምተዋል። ተማሪዎቹ ከትምህርት ቤት  በመውጣት ታፔላዎችን እየነቃቀሉ መጣላቸውን፣ የወረዳው አስተዳዳሪን መኪና በድንጋይ መሰባበራቸውን እንዲሁም አቶ ቡርቃ ደምቢ የተባሉትን የወረዳው የኦህዴድ መሰረታዊ ድርጅት አደራጅን መደብደባቸውን ከስፍራው የደረሰን መረጃ አመልክቷል። ተማሪዎቹ ድርጊቱን ሲፈጽሙ ...

Read More »

ቤታቸው የፈረሰባቸው በርካታ የጎነደር ነዋሪዎች ምሬታቸውን ገለጹ

ሚያዚያ ፰ (ስምንት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በዛሬው እለት አዘዞ አይራ ቀበሌ አካባቢ  ቀበሌ በብዙ መቶዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎች ቤታቸው በጉልበት ፈርሶባቸዋል። ነዋሪዎች ቤተሰቦቻቸውን ይዘው ሜዳ ላይ የወደቁ ሲሆን፣ በዝናብና በጸሃይ እየተቸገሩ መሆኑንም ገልጸዋል። በነዋሪዎችና በፖሊስ መካከል መጠነኛ የሆነ ግጭት ተከስቶ እንደነበር ነዋሪዎች ተናግረዋል። አንዳንድ ነዋሪዎች ተስፋ በመቁረጥ በራሳቸው ላይ እርምጃ መውሰዳቸውን ነዋሪዎች ይገልጻሉ። በባህርዳር ከሳምንት በፊት ከ600 በላይ ህገ ...

Read More »

ሰማያዊ ፓርቲ በፌደራል መንግስቱና በቡለን ወረዳ ላይ የመሰረተው ክስ ሊታይ ነው

ሚያዚያ ፰ (ስምንት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በቤንሻንጉል ጉምዝ በህገ ወጥ መንገድ የተፈናቀሉ ኢትዮጵያውያን ወደ ቦታቸው በአስቸኳይ እንዲመለሱና ተገቢው ካሳ እንዲከፈላቸው እንዲደረግ በታዋቂው የአለማቀፍ ህግ ባለሙያ ዶ/ር ያዕቆም ሃይለማርያም አማካኝነት ክስ የመሰረተ ሲሆን፣ ክሱ ሃሙስ ሚያዝያ 9/2006ዓ/ም በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ስምንተኛ ፍትሃ ብሄር ችሎት ላይ መታየት ይጀምራል። ፓርቲው የቡለን ወረዳ ቀኑን ጠቅሶ ‹‹ስለምትፈናቀሉ ልቀቁ!›› ያለበትን ማስታወቂያና ማስጠንቀቂያዎች በመረጃነት ...

Read More »

በኢትዮጵያ ስራ የጀመሩ የውጭ ባለሃብቶች ቁጥር አነስተኛ ነው ተባለ

ሚያዚያ ፰ (ስምንት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በኢትዮጵያ ባለፉት ሶስት ዓመታት ወደ ኢንቨስትመንት ለመግባት ፈቃድ ከወሰዱት የውጭ አገር ባለሃብቶች መካከል ወደሥራ የገቡት ከግማሽ በታች መሆናቸውን ከኢንቨስትመንት ባለስልጣን የተገኘ መረጃ አመልክቷል፡፡ ባለፉት ሶስት ዓመታት 187 ነጥብ 31 ቢሊየን ብር ካፒታል ያላቸው 2ሺህ 164 ያህል የውጭ ባለሃብት ፈቃድ የተሰጣቸው ሲሆን  እስካሁን 50 ቢሊየን ብር  ካፒታል ያስመዘገቡ 770 ባለሃብቶች ማለትም ካፒታላቸው 28 ...

Read More »

የአቶ አስገደ ገብረስላሴ ልጅ ተፈረደበት

ሚያዚያ ፰ (ስምንት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የታዋቂው ፖለቲከኛ የአቶ አስገደ ልጅ አህፎም ስገደ ያለ በቂ ምክንያት በተለያዩ እስር ቤቶች እየተዘዋወረ ሲታሰር ከቆየ በሁዋላ ፍርድ ቤት በ4 አመት ከአምስት ወር እስራት እንዲታሰር ፍርዶበታል። አህፎም ፎርጅድ ሰርተፊኬት ሰርቷል ተብሎ ክስ የተመሰረተበት ሲሆን፣ አቃቢ ህግ ምንም አይነት ማስረጃ ሳያቀርብ ፍርድ ቤት ውሳኔ ማስተላለፉ ብዙዎችን አስገርሟል። አቶ አስገደ ገብረስላሴ ህወሃት አዲስ አበባን ...

Read More »

ኢህአዴግ የ2007 ምርጫ ማሸነፊያ ስትራቴጂዎችን አወጣ

ሚያዚያ ፯ (ሰባት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከኢህአዴግ የውስጥ ምንጮች ለኢሳት የተላከው የ2007 ዓም ምርጫ ማስፈጸሚያ እቅድ እንደሚያሳየው ለአርሶ አደሩ የማዳበሪያ እዳ እፎይታ በ2006/2007 የመኸር ምርት ዘመን የሚሰጥ ሲሆን፣ ለከተማ ነዋሪዎች ደግሞ  በ20 ሺ ብር ቅድመ ክፍያ ለመኖሪያ ቤት ግንባታ የሚውሉ ቦታዎችን ይሰጣል። 20 ሺ ብር የቅድመ ክፍያ ገንዘብ ለማቅረብ ለማይችሉት የከተማ ነዋሪዎች  የምርጫ ቅስቀሳ በሚካሄድባቸው ወራት ከባንክ በብድር ...

Read More »

ሰማያዊ ፓርቲ ታላቅ ህዝባዊ ተቃውሞ ማዘጋጀቱን አስታወቀ

ሚያዚያ ፯ (ሰባት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ፓርቲው ” ሰላማዊ ትግላችንን አጠናክረን በመቀጠል የተነጠቁ መብቶቻችንን እናስመልሳለን፡” በሚል ርእስ ባወጣው መግለጫ ” ሰማያዊ ፓርቲ በመንግስት የሚፈጽሙ ሕገ ወጥ ድርጊቶች የሠብአዊና ዲሞክራሲያዊ መብት ጥሰቶች እንዲቆሙ ለመንግስት አካላት በተደጋጋሚ ጊዜያት ጥሪ ቢያቀርብም የሚሰማው ማጣቱን ገልጿል። በአገሪቱ የሚታዩ ችግሮች በአስቸኳይ እንዲፈቱ ለማድረግ  እሁድ ሚያዚያ 19/2006 ዓ.ም ከጠዋቱ 4 ሰዓት እስከ 8 ሰዓት የሚቆይ ...

Read More »

የሶማሊ ክልል ፕሬዚዳንት ከስልጣን የምነሳ ከሆነ ክልሉ የራሱን እድል በራሱ ይወስናል አሉ

ሚያዚያ ፯ (ሰባት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢህአዴግ ምክር ቤት በሶማሊ ክልል የሚፈጸመው ከፍተኛ የሰብአዊ መብት ጥሰት በክልሉ ያሉትን ባለስልጣኖች ብቻ ሳይሆን በአጠቃላይ የኢህአዴግን ባለስልጣኖችን በአለማቀፍ የወንጀል ፍርድ ቤት የሚያስጠይቅ መሆኑን ድምዳሜ ላይ የደረሰው ኢህአዴግ፣  ፕሬዚዳንት አብዲ ሞሃመድ ኡመርን ለማውረድ እንቅስቃሴ መጀመሩ  ፕሬዚዳንቱ ይህንን ንግግር እንዲናገሩ እንዳደረጋቸው ምንጮች ገልጸዋል። አቶ አብዲ   የእርሳቸው ታማኝ ደጋፊ የሆኑ በውጭ አገራት የሚኖሩ የክልሉን ...

Read More »

በምርጥ ዘር ጥራት መጓደል ምክንያት ከፍተኛ ሃብት እየባከነ ነው ተባለ

ሚያዚያ ፯ (ሰባት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢትዮጵያ ምርጥ ዘር ድርጅት እንዳስታወቀው ባለፉት አመታት ለአርሶደሩ የቀረቡ የምርጥ ዘር ማሻሻያ ዝርያዎች የመብቀልና ምርት የማፍራት ችግር ገጥሞአቸዋል። በዚህም የተነሳ በየአመቱ ከ150 ሺ ኩንታል በላይ ምርጥ ዘር ለብክነት እየተዳረገ ነው። በዚህ አመት ብቻ 25 ሺ 97 ኩንታል ምርት ዘር ባክኖ መቅረቱን ድርጅቱ አስታውቋል። በየዓመቱ ጥራታቸውን ያልጠበቁ ዝርያዎች ያለአግባብ እየቀረቡ ከ2ዐሽ ሄከታር በላይ ...

Read More »

በደቡብ ሱዳን የሚካሄደው ጦርነት እንደገና አገረሸ

ሚያዚያ ፯ (ሰባት) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በአዲስ አበባ ሲካሄድ የነበረው የደቡብ ሱዳን የሰላም ድርድር ውጤት አለማምጣቱን የሚያሳይ ጦርነት በነዳጅ ሃብቷ በበለጸገቸው የቤንቲዩ ግዛት መጀመሩን ዘገባዎች የመለክታሉ። በሪክ ማቻር የሚመራው የአማጽያኑ ሃይል ቤንቲዩን መቆጣጠሩን ሲያስታውቅ፣ የፕሬዚዳንት ሳልቫኪር መንግስት ደግሞ ዜናውን አስተባብሎአል። እንደገና ባገረሸው ጦርነት አመጽያኑ ድል እንዳገኙና በመሸሽ ላይ ያሉትን የመንግስት ወታደሮች እየተከታተሉ በመውጋት ላይ መሆናቸውን እየገለጹ ነው። የተባበሩት ...

Read More »