ግብረሰዶማዊያንን የሚመለከተው አንቀጽ ወጥቶ የይቅርታ አሰጣጡን የሚያሻሽለውን ረቂቅ አዋጅ አጸደቀ

ሚያዚያ ፳፪ (ሃያ ሁለት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሥራ ላይ የነበረውን የይቅርታ አሰጣጥና አፈጻጸም ሥነሥርዓት የሚያሻሽለው ረቂቅ አዋጅ ይቅርታ ከማያሰጡ ወንጀሎች መካከል የግብረሰዶም ጉዳይ አንዱ አድርጎ ቢያቀርብም፣ በአቶ አስመላሽ ወ/ስላሴ የሚመራው የፓርላማው የህግ ፣ፍትህና አስተዳዳር ጉዳዮች ቋሚ ኮምቴ የግብረሰዶማዊያን ጉዳይ ከዝርዝሩ እንዲወጣ በማድረግ ሕጉን ትላንት እንዲጸድቅ አደርጓል፡፡ በፍትህ ሚኒስቴር ተረቅቆ በሚኒስትሮች ምክርቤት ጸድቆ፤  በ99 በመቶ በኢህአዴግ አባላት ለተያዘው ፓርላማ መጋቢት ...

Read More »

ሙሉጌታ ዘውዴ ለሁለተኛ ጊዜ በኖርዌይ የተዘጋጀውን የማራቶን ሩጫ አሸነፈ

ሚያዚያ ፳፪ (ሃያ ሁለት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በየዓመቱ በሚዘጋጀውን የበርገን ማራቶን ለሁለተኛ ጊዜ ያሸነፈው ሙሉጌታ፣ የኢሳት አርማ ያለበትን ቲሸርት ለብሶ በመሮጥ ለኢሳት ያለውን አድናቆትና ድጋፍ ገልጿል። ኢትዮጵያዊው አትሌት በኢትዮጵያ በግፍ የታሰሩ የፖለቲካ እስረኞች እንዲፈቱ ፣ ኖረዌይ የህወሃትን መንግስት መርዳቱዋን እንድታቆም ጠይቋል። ሙሉጌታ ውድድሩን በ 1.09.02. ጨርሷል። ኢሳት 4ኛ አመቱን በማክበር ላይ ባለበት ወቅት ሙሉጌታ ዘውዴ ያሳየው ድጋፍ የኢሳት ቤተሰቦችንና ...

Read More »

በገንዳሆ ከተማ በህዝቡና በፖሊስ መካከል በተፈጠረ ግጭት 4 ሰዎች ተገደሉ

ሚያዚያ ፳፩ (ሃያአንድ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በሰሜን ጎንደር ዞን በመተማ ወረዳ በገንዳሆ ከተማ አንድ በጉምሩክ በኩል ውክልና ያለው የፌደራል ፖሊስ አንዱን የባጃጅ ሹፌር ” ኮንትሮባንድ ጨርቅ ጭነሃልና ጉቦ ሰጥተኸኝ እለፍ” በማለቱና ሾፌሩም “ለዚህ ለማይረባ ጨርቅ ጉቦ አልከፍልህም” የሚል መልስ በመስጠቱ ፖሊሱ ሾፌሩን ተኩሶ መግደሉን የአካባቢው ነዋሪዎች ለኢሳት ገልጸዋል። በድርጊቱ የተበሳጨው የገንዳውሃ ህዝብ ወደ ወረዳው ፖሊስ ጣቢያ በመሄድ  ገዳዩ ለፍርድ ...

Read More »

የሰማያዊ ፓርቲ ወጣት አመራሮችና ደጋፊዎች በዋስ እንደማይፈቱ አስታወቁ

ሚያዚያ ፳፩ (ሃያአንድ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የፓርቲውን ምክትል ሊ/መንበር አቶ ስለሺ ፈይሳንና የህዝብ ግንኑነት ሃላፊውን ብርሃኑ ተክለያሬድን ጨምሮ ከ20 በላይ አመራሮችና ደጋፊዎች ትናንት ፍርድ ቤት ቀርበው ፣ ፍርድ ቤቱ ፖሊስ ክስ እንዲመሰርት ወይም እስረኞቹ በዋስ እንዲለቀቁ ቢያዝዝም እስረኞቹ ሃሳቡን ሳይቀበሉት ቀርተዋል። እስረኞቹ “ሰልፉ ህጋዊ እውቅና አግኝቶ በመገናኛ ብዙሃንም የተዘገበ በመሆኑ ፖሊስ ህገወጥ ሰልፍ አድርገዋል በሚል ለፍርድ ቤቱ ያቀረበው ክስ ...

Read More »

 በዞን ዘጠኝ ጦማርያን እና በጋዜጠኞች ላይ የተወሰደው የእስር እርምጃ እንዳሣሰበው ሲ.ፒ.ጄ ገለጸ።

ሚያዚያ ፳፩ (ሃያአንድ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ዓለማቀፉ የጋሴጠኞች ተንከባካቢ ድርጅት(ሲፒጄ)  ባወጣው መግለጫ የኢትዮጵያ መንግስት ሰሞኑን በ9 ጸሀፍያን ላይ የወሰደው የእስር እርምጃ፤ ሀሳብን በነፃነት የመግለጽ መብት ላይ ከተቃጡ የከፉ እርምጃዎች አንዱ ነው ብሏል። “የኢትዮጵያ ባለስልጣናት በሰላማዊ መንገድ ሀሳብን መግለጽን እንደወንጀል እየቆጠሩት ነው” በማለት ነው -የሲፒጄ የምስራቅ አፍሪቃ ወኪል-ቶም ሩድስ-እርምጃውን የኮነኑት። እሁድ ዕለት የመንግስት አቃቤ ህግ በ አዲስ ጉዳይ ዋና አዘጋጅ ...

Read More »

አሜሪካ እና አውሮፓ በሩስያ ላይ ተጨማሪ ማእቀብ ጣሉ

ሚያዚያ ፳፩ (ሃያአንድ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ሩስያ በዩክሬን የሚታየውን ችግር ለማስቆም አልቻለችም በሚል አሜሪካና የአውሮፓ ህብረት በሩስያ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ተቋማትና ለፕሬዚዳንት ፑቲን ቅርበት አላቸው በሚሏቸው ባለስልጣናት ላይ ማእቀብ ጥለዋል። ሩሲያ ድርጊቱን አጥብቃ ተቃውማለች። በዩክሬን ምስራቃዊ ክፍል የተነሳው አመጽ አሁንም እንደቀጠለ ነው። ብዙዎች ህዝበ ውሳኔ እንዲደረግ እየጠየቁ ሲሆን፣ ሩሲያ ዩክሬንን ትወር ይሆናል የሚለውን ስጋት አጠናክሮታል።

Read More »

የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች መንግስት ያዘጋጀውን የአዲስ አበባ ካርታ እየተቃወሙ ነው

ሚያዚያ ፳ (ሃያ) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የአዲስ አበባ መስተዳደር የከተማዋን የመሬት ችግር ይቀርፋል በሚል ያዘጋጀውን አዲስ ካርታ በአምቦ፣ በጅማ፣ በነቀምት እና በተለያዩ ዩኒቨርስቲዎች የሚማሩ ተማሪዎች እየተቃወሙት ነው። በወለጋ የፌደራል ፖሊስ አባላት በወሰዱት እርምጃ በተማሪዎች ላይ ጉዳት ደርሷል። ተቃውሞውን በተመለከተ ጥያቄ ያቀረብንላቸው የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ምክትል ሊቀመንበርና የቀድሞ የፓርላማ አባል አቶ ገብሩ ገብረማርያም አቅጣጫ የያዘ ይሁን አይሁን ባይታወቅም ተቃውሞዎች ...

Read More »

ኢትዮጵያ የታሰሩ ጋዜጠኞችና ጸሃፊዎችን እንድትፈታ ሂውማን ራይትስ ወች ጠየቀ

ሚያዚያ ፳ (ሃያ) ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-መንግስት ተጨባጭ ማስረጃ እስካላመጣ ድረስ ከ3 ቀናት በፊት ያሰራቸውን 3 ጋዜጠኞች እና 6 ጸሃፊዎችን በአስቸኳይ እንዲፈታ የሰብአዊ መብት ድርጅቱ አሳስቧል፡፡ ኢትዮጵያን የሚጎበኙት የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ተጠሪ ጆን ኬሪ ፍትሃዊ ባልሆነ ዳኝነት በእስር የሚሰቃዩ ጋዜጠኞች እንዲሁም ያለበቂ ማስረጃ የሚታሰሩት ጋዜጠኞች እና የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች እንዲፈቱ በኢትዮጵያ መንግስት ላይ ጫና እንዲያሳድሩ ሂውማን ራይትስ ወች ...

Read More »

ሰማያዊ ፓርቲ የተሳካ የተቃውሞ ሰልፍ አካሄደ

ሚያዚያ ፳ (ሃያ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ሚያዚያ 19 በአዲስ አበባ የተካሄደ ውን የተቃውሞ ሰልፍ ለመዘገብ በስፍራው የተገኘው ዘጋቢያችን በሰልፉ  ላይ የሰማያዊ ፓርቲ ወጣት አመራሮች እና ደጋፊዎች  በብዛት መገኘታቸውን ገልጿል። ወጣቶቹ የነበራቸው ጽናት የሚገርም ነበር ያለው ዘጋቢያችን፣ ፖሊስ በሰልፉ ላይ ህዝብ በብዛት እንዳይገኝ ለማድረግ ያሰበው እቅድ አለመሳካቱንም ገልጿል። ሰልፈኞች በርካታ ፖሊቲካዊና ማህበራዊ ጥያቄዎችን እያነሱ ሲጠይቁ መመልከቱንም ገልጿል። ሰማያዊ ፓርቲ ከ25 ...

Read More »

የአሜረካው ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጆን ኬረይ በስልክ ከፐሬዚዳንት ሳልቫኪር ጋርመነጋገራቸው ታወቀ::

ሚያዚያ ፳ (ሃያ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ጆንኬሪበደቡብሱዳንእየተካሄደያለውጦርነትእንዳሳሰባቸውናበተለይበቤንቲዩናበቦር   የተካሄደውየሰላማዊሰዎችግድያ የሚወገዝ መሆኑን ገልጸው፣ድርጊቱንየፈጸሙትለፍርድእንዲቀርቡም ጠይቀዋል። ጆንኬሪና  ሳልቫኬር  በንግግራቸውወቅት የኢጋድየሰላምሂደቱንእንደሚደግፉሲገልጹ፣  በተለይየተባበሩትመንግስታት ድርጅት እየሰጠያለውንአስተዋጾአድንቀዋል::

Read More »