ምርጫ ቦርድ “ኢህአዴግ መቶ በመቶ አሸንፏል” ሲል የመጨረሻ ቡራኬውን ሰጠ

ሰኔ ፲፭ (አስራ አምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ምርጫ ቦርድ ጊዚያዊ ውጤቱን ይፋ ባደረገበት ወቅት የ105 ወንበሮችን ጉዳይ ግልጽ ባለማድረጉ አንዳንዶች “ኢህአዴግ ለተቃዋሚዎች ለመካፋፈል አስቦ ያደረገው ሊሆን ይችላል” በማለት አስተያየት ሲሰጡ ቢቆዩም፣ ቦርዱ ግን ኢህአዴግ መቶ በመቶ ምርጫውን አሸንፋል በማለት የመጨረሻ ውሳኔውን ሰጥቷል። ዋናዎቹ የተቃዋሚ ድርጅቶች ሰማያዊ ፓርቲና መድረክ ምርጫውን ” አሳፋሪ” ነው ሲሉ አጣጥለውታል።በአፍሪካ ምርጫን 100 በመቶ ...

Read More »

ፍርድ ቤት አቶ ማሙሸት አማረ ዋስትና ተከልክለው ወደ ቅሊንጦ እንዲላኩ ወሰነ

ሰኔ ፲፭ (አስራ አምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ችሎቱን የተከታተሉት በአቶ ማሙሸት የሚመራው መኢአድ ምክትል ህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ለኢሳት እንደገለጹት አቶ ማሙሸት፣ ሰኔ 10፣ 2007 ዓም በ5 ሺ ብር ዋስ እንዲወጣ ፍርድ ቤት የወሰነ ቢሆንም፣ ፖሊስ ለመልቀቅ ፈቃደኛ ሳይሆን ቀርቶ ዛሬ ፍርድ ቤት አቅርቦታል። ፖሊስ፣ አቶ ማሙሸት ቢፈታ በምስክሮቼ ላይ ዛቻና ማስፈራሪያ ሊያደርስባቸው ይችላል የሚል ይጋባኝ ያቀረበ ሲሆን፣ ...

Read More »

የአዲስ አበባ ባለታክሲዎች በግዳጅ ቦንድ እንዲገዙ ታዘዙ።

ሰኔ ፲፭ (አስራ አምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ከሰሞኑ በአዲስ አበባ የሚገኙ የታክሲ አገልግሎት ሰጪ የግል ባለንብረቶች ወደ አዲስ አበባ መንገድ ትራንስፖርት ጽ/ቤቶች ታፔላ ለመቀየር በሄዱበት ወቅት ከተለመደው የታፔላ ማስቀየሪያ አገልግሎት ክፍያ ውጪ ባልተጠበቀ ሁኔታ የ1ሺ ብር ቦንድ ካልገዛችሁ የሚል ግዳጅ ተጥሎባቸዋል ። “አሁንስ ወዴት እንሂድ? ለማን አቤት እንበል?” በማለት የታክሲ ባለንብረቶች ሲያማርሩ ተሰምተዋል። ታክሲዎች ለ3 ወራት ያክል ...

Read More »

በተለያዩ የአውሮፓ ከተሞች የተቃውሞ ሰልፎች ሊደረጉ ነው

ሰኔ ፲፭ (አስራ አምስት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- አቶ አንዳርጋቸውን ጨምሮ ሌሎች በእስር ላይ ያሉ ፖለቲከኞች፣ ጋዜጠኞች፣ የሙስሊም የመፍትሄ አፈላላጊ የኮሚቴ አባላትና የሲቪክ ማህበረሰብ አባላት እንዲፈቱ የሚጠይቅ የተቃውሞ ሰልፍ በተለያዩ የአውሮፓ ከተሞች ከዛሬ ምሽት ጀምሮ ይካሄዳል። በጀርመን በፍራንክፈርት፣ሙኒክ፣ዱስልዶርፍ እና በርሊን የሚካሄድ ሲሆን፣ በፍራንክፈርት የሚደረገው ተቃውሞ ለ24 ሰአታት ይቆያል። በጣሊያን ሮማ፣ በቤልጂየም ብራሰልስ፣ በእንግሊዝ ለንደንና በኖርዌይ ኦስሎ የተቃወሞ ሰልፎች ...

Read More »

ምርጫውን ተከትሎ በኦሮምያ ብቻ ከ600 በላይ የመድረክ አባላት ታስረዋል

ሰኔ ፲፪ (አስራ ሁለት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- በብዙዎች ዘንድ አስቂኝ ተብሎ የተተቸውን የ2007 ዓም ምርጫ ተከትሎ በኦሮምያ ብቻ ከ640 በላይ የመድረክ ደጋፊዎች ሲታሰሩ፣ 66 በድብደባ ጉዳት ደርሶባቸዋል፣7 አባለት በጥይት ቆሰልዋል፣ 2 አባላት ደግሞ መገደላቸውን መድረክ አስታውቋል። ከምርጫው ጋር በተያያዘ የሚታሰሩ ሰዎች ቁጥር በሺዎች እንደሚቆጠር መረጃዎች ያመለክታሉ። መድረክ እንዳለው በምርጫ 2007 ማግሥት በመድረክ አባላት ላይ የሚፈጸሙት የማዋከብና የማሰቃየት ...

Read More »

ከምርጫው ጋር በተያያዘ በምስራቅ ጎጃም የደህንነት ሃላፊ ሆኖ የተሾመው የህወሃት አባል ነው ተባለ

ሰኔ ፲፪ (አስራ ሁለት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በክረምቱ ወቅት 119 የሚሆኑ የብአዴን አባላት በድሬዳዋ ከተማ የደህንነት እና መረጃ መሰብሰብ ስልጠና ተሰጥቷቸው በክልሉ ከተሰማሩት መካካል አንዱ የሆነው ሰራተኛው እንደገለጸው፣ ማንኛውም ደህህነት ሰራተኛ የስለላ ሪፖርቱን ተክሌ ለተባለ የደህንነት ሰራተኛ ሲያቀርብ መቆየቱን ለኢሳት ተናግሯል። ስልጠናውን ከወሰዱት የደህንነት ስራተኞች መካከል አንዳንዶች በምስራቅ ጎጃም ደብረማርቆስ ከተማ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ሆነው በመመዝገብ መረጃዎችን ሲያስተላልፉ፣ ...

Read More »

በግል የጤና ተቋማት ላይ ትችት ቀረበ

ሰኔ ፲፪ (አስራ ሁለት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የማህበራዊ ጥናት መድረክ በቅርቡ ባካሄደው ጥናት በአዲስአበባ የግሉ የጤና ዘርፍ ከፍተኛ የጥራት መጓደልን ይዞ የተጋነነ የአገልግሎት ክፍያ እየጠየቀ መሆኑን ገልጿል። ጥናቱ በአዲስአበባ ከሚገኙ ክሊኒኮችና ሆስፒታሎች መካከል በ34ቱ ላይ ያተኮረ ሲሆን አገልግሎት ክፍያ (ዋጋን) በተመለከተ በመንግስት ሆስፒታሎች የካርድ ክፍያ አማካይ ዋጋ 5 ብር ሲሆን፣ በግል ክሊኒኮች አማካይ ዋጋ 100 ብር ነው፡፡ ...

Read More »

ከምርጫው በሁዋላ መንግስት “የበቀል ጅራፉን” እያሳረፈብን ነው ሲሉ የደቡብ ክልል የተቃዋሚ አባላት ተናገሩ

ሰኔ ፲፩ (አስራ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ምርጫው በአሳፋሪ ሁኔታ መጠናቀቁን ተከትሎ የመንግስት የጸጥታ ሃይሎች የመድረክ ደጋፊዎችን ቤቶች መቃጠላቸውን፣ መደብደባቸውንና ማሳደዳቸውን የአርባምንጭ ነዋሪዎች ተናግረዋል። በተለይ በላካ ቀበሌ ብዙ ሰዎች አካላ ጎደሎ ሆነዋል፣ ቤቶቻቸውም ተቃጥሎባቸዋል የሚሉት ነዋሪዎች፣ የቀበሌ አመራሮች ከሰኔ 15 በሁዋላ መግቢያችሁን ፈልጉ እየተባሉ መሆኑን ገልጸዋል። አቶ ዳዊት ጉበዜ እና አዛውንት እናቱ ወ/ሮ ሃማሜ ሃይሉ ክፉኛ ተደብድበው ሆስፒታል ...

Read More »

ፍርድ ቤት አቶ ማሙሸት አማረን ይፈቱ ቢልም ፖሊስ ግን አለቅም አለ

ሰኔ ፲፩ (አስራ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በምርጫ ቦርድ የታገደው የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት ( መኢአድ ) ፕሬዝደንት የሆኑት አቶ ማሙሸት አማረ ከሳምንታት እስር በሁዋላ በ5 ሺ ብር ዋስ እንዲፈቱ ፍርድ ቤት ውሳኔ ቢያስተላልፍም፣ ውሳኔው ለሁለተኛ ጊዜ በፓሊስ ተጥሶ ወደ እስር ቤት ተወስደዋል። ግንቦት 26/2007 ቦሌ የሚገኘው ችሎት አቶ ማሙሸት የቀረበባቸው ክስ እንደማያስከስሳቸው በመግለጽ እንዲፈቱ ቢወስንም፣ ፖሊስ በራሱ ...

Read More »

ወጣት ሳሙኤል አወቀ በመንግስት ታጣቂዎች መገደሉን ሰማያዊ ፓርቲ አስታወቀ

ሰኔ ፲፩ (አስራ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ፓርቲው ” የሰማዕታት ደም ይጮሃል፤ ይጣራል” በሚል ርእስ ባወጣው መግለጫ ፣ ወንጀሉን የፈጸሙት የመንግስት አካላት ናቸው ብሎአል። ወንጀለኞች ለፍርድ ይቅረቡ ብሎ እንደማይጠይቅም አስታውቋል። “ሰኔ 8 ቀን 2007 ዓ.ም በደብረ ማርቆስ ከተማ እጅግ በሚሰቀጥጥ ጭካኔ እንደ እባብ ተቀጥቅጦ የተገደላው የሰማያዊ ፓርቲ ቆራጥ ታጋይ ሳሙኤል አወቀ የስርዓቱ አገልጋዩች ለዓመታት ሲያስፈራሩት፣ ሲደበድቡት፣ ሰርቶ የመኖር ...

Read More »