የተከሰቱ ግጭቶችን የሚመረምር ቡድን ተሰማራ

(ኢሳት ዲሲ–ሕዳር 25/2011) በኢትዮጵያ በተለያዩ አከባቢዎች የተከሰቱ ግጭቶችን የሚመረምር ቡድን ማሰማራቱን ጠቅላይ አቃቤህግ አስታወቀ። በእነዚህ ግጭት በተከሰተባቸው አካባቢዎች እጃቸውን ያስገቡ አካላትን የመለየት ስራ የሚያከናውን የመርማሪ ቡድን እንደሆነም ተመልክቷል። በተደራጀ የኢኮኖሚ አሻጥር፣ሌብነትና፣ የሰብአዊ መብት ጥሰት የተሳተፉ ሕገ-ወጦችን ወደ ሕግ የማቅረቡ ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የጠቀሰው የፌደራል ጠቅላይ ዓቃቤ ህግ የምርመራ ውጤቱን ለህብ በይፋ እንደሚያሳውቅም ገልጿል። በየቦታው ግጭት አለ። በማንነትና በወሰን ይገባኛል መነሻ ...

Read More »

በኦሮሚያ ክልል ከተሞች ትዕይንተ ህዝብ ተካሄደ

(ኢሳት ዲሲ–ሕዳር 25/2011)በተለያዩ የኦሮሚያ ክልል ከተሞች ግድያና መፈናቀል እንዲቆም የሚጠይቅ ትዕይንተ ህዝብ ተካሄደ። ካለፈው ቅዳሜ ጀምሮ በወለጋ፣ ምዕራብ ሸዋና ኢሉባቡር እየተደረጉ ያሉት ሰልፎች መንግስት አስቸኳይ የሆነ እርምጃ በመውሰድ በኦሮሞ ህዝብ ላይ የተጋረጠውን አደጋ እንዲያስቆም የሚጠይቁ ናቸው። በቅርቡ በቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል አዋሳኝ በሆኑ የምስራቅ ወለጋ አካባቢዎች በተፈጸመ ጥቃት በርካታ ፖሊሶችና ሰላማዊ ዜጎች መገደላቸውን ተከትሎ ህዝቡ ተቃውሞን እያሰማ ይገኛል። በቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል ...

Read More »

የአማራ እና የኦሮሞ ህዝቦች ግንኙነት የበለጠ መጠናከር አለበት ተባለ

(ኢሳት ዲሲ–ሕዳር 24/2011)የኢትዮጵያ ችግር ከስረ መሰረቱ እንዲነቀል የአማራ እና የኦሮሞ ህዝቦች ግንኙነት የበለጠ መጠናከር እንዳለበት የአማራ ክልል ፕሬዝዳንት ገዱ አንዳርጋቸው ገለጹ። በአቶ ገዱ አንዳርጋቸው የተመራው የአማራ ክልል የልኡካን ቡድን በዋሽንግተን ዲሲ አካባቢ ካለው የአማራ ተወላጆችና የአማራ ጉዳይ ያገባናል ካሉ ኢትዮጵያዊያን እና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ጋር ምክክር አድርገዋል። ከስብሰባው ተዳሚዎች ለቀረቡ ጥያቄዎችም ምላሽ ሰጥተዋል። የኢትዮጵያ ችግር ከስረ መሰረቱ እንዲነቀል የእነዚህ ህዝቦች ግንኙነት ...

Read More »

በአሶሳ ዩኒቨርስቲ ባሉት ተማሪዎች ትምህርት ተጀመረ

(ኢሳት ዲሲ–ሕዳር 24/2011) በአሶሳ ዩኒቨርስቲ ተቋርጦ የነበረው የመማር ማስተማር ሒደት ባሉት ተማሪዎች መጀመሩ ታወቀ። ኢሳት ወደ ዩኒቨርስቲው ተማሪዎች ደውሎ እንዳገኘው መረጃ ከሆነ በግቢው ውስጥ አብዛኛው ተማሪ ባይኖርም ያሉትን ተማሪዎች አሰባስቦ ለማስተማር እየተሞከረ ነው። ተማሪዎቹ እንደሚሉት ከሆነ በግቢው ውስጥ ብዙ ተማሪ ካለመኖሩ የተነሳ ሁለት ክፍሎችን በአንድ ላይ አጥፎ ነው ትምህርቱ እንዲሰጥ እየተደረገ ያለው። እንደነሱ አባባል ከሆነም ዩኒቨርስቲው ትምህርቱን ሲጀምር ምናልባትም ግቢውን ...

Read More »

የወልቂጤ አካባቢ ወጣቶች በልዩ ሃይል እየታፈሱ ነው ተባለ

(ኢሳት ዲሲ–ሕዳር 24/2011) በጉራጌ ዞን የወልቂጤ አካባቢ ወጣቶች በአካባቢው ልዩ ሃይል እየታፈሱ መሆኑ ተሰማ። በጉራጌና በቀቤና ብሔረሰቦች መካከል ቀደም ሲል ተቀስቅሶ የነበረው ግጭትም አሳሳቢ ወደሚባል ደረጃ እየተሸጋገረ መሆኑን ኢሳት ወደ አካባቢው ደውሎ ያገኘው መረጃ ያመለክታል። በፌደራል ደረጃ ጉዳዩን ለመፍታት የተደረገው ሙከራ ሊሳካ አልቻለም የሚሉት የኢሳት ምንጮች ግጭቱ እንዲባባስ የሚፈልጉ አካላት ደግሞ በአካባቢው ውጥረት እየፈጠሩ ነው ብለዋል። ሁኔታውን ለማረጋጋት የፌደራሉ መከላከያ ...

Read More »

በቤንሻንጉልና ኦሮሚያ አዋሳኝ አካባቢዎች ጥቃት የሚፈጽመው ኦነግ ነው ተባለ

(ኢሳት ዲሲ–ሕዳር 24/2011) በቤንሻንጉል ጉምዝና ኦሮሚያ ክልሎች አዋሳኝ አካባቢዎች ጥቃት በመፈጸም ላይ ያለው የኦነግ ጦር መሆኑን የቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል አስታወቀ። ለእርዳታ የተዘጋጀ ከ2ሚሊዮን ብር በላይ በታጣቂዎች መዘረፉም ታውቋል። በሁለቱ ክልሎች መካከል የተፈጠረው ውጥረት ቀጥሏል። መከላከያ ሰራዊትና የፌደራል ፖሊስ በግጭቱ አካባቢዎች መስፈራቸውን የቤንሻንጉል ጉምዝ ፖሊስ ኮሚሽነር አቶ ሰይፈዲን ሀሩን  ለኢሳት ገልጸዋል። ለውጡን ለማደናቀፍና ኦሮሚያ ክልልን የጦርነት ዓውድማ የማድረግ ዕቅድ መኖሩን የኦሮሞ ...

Read More »

በአፋር ክልል በተቀሰቀሰ ግጭት አንድ የአፋር ወጣት ተገደለ

(ኢሳት ዲሲ–ሕዳር 24/2011) በአፋር ክልል በመሬት ይገባኛል ጥያቄ ኤል ውሃ አካባቢ ቡርካ በሚባል ቦታ በተቀሰቀሰ ግጭት ሰላም ለማስከበር በሚል ጣልቃ በገባ የመከላከያ ሰራዊት አንድ የአፋር ወጣት መገደሉን ለኢሳት የደረሰ መረጃ አመልክቷል። በአፋር ዛሬ የሚጀመረውንና አብዛኛውን አመራሮችን ያሰናብታል ተብሎ የሚጠበቀው የክልሉ ገዢ ፓርቲ ጉባዔውን በሚያካሂድበት ወቅት ዋዜማ የተቀሰቀሰው ግጭት ሶስተኛ ቀኑን መያዙ ታውቋል። ጉባዔውን በሁከት በማጀብ የአቶ ስዩም አወል ቡድን የሚፈጽመው ...

Read More »

በኦሮሚያና ቤንሻንጉል ጉምዝ አዋሳኝ በርካታ የፖሊስ አባላትና ነዋሪዎች ተገደሉ

(ኢሳት ዲሲ–ሕዳር 20/2011)በኦሮሚያና ቤንሻንጉል ጉምዝ አዋሳኝ መንደሮች በተነሳ ግጭት በርካታ የፖሊስ አባላትና እንዲሁም ነዋሪዎች መገደላቸው ተገለጸ። የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ኮሚኒኬሽን ቢሮ እንዳስታወቀው በምስራቅ ወለጋ ሊሙ ወረዳ በተከሰተው ግጭት ከፍተኛ የንብረት ውድመትም ተከስቷል። ስልጣን ያለአግባብ ሲጠቀሙ ፣ የኢኮኖሚ ዝርፊያ ሲያካሂዱ የነበሩና ይህ ጥቅማቸው ከእጃቸው የወጣ አካላት ትግሉን ወደ ኋላ ለመመለስ በሁሉም ስፍራዎች ግጭቶች እንዲከሰቱ እያደረጉ ነው ሲል የኦሮሞ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ ኦዴፓ ...

Read More »

የሰላም እና የአስተዳደር ኮሚሽኖችን ለማቋቋም የተረቀቀ አዋጅ ቀረበ

(ኢሳት ዲሲ–ሕዳር 20/2011) የሰላም እና የአስተዳደር  ወሰንን የተመለከቱ ኮሚሽኖችን ለማቋቋም የተረቀቀ አዋጅ ዛሬ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀረበ። በኢትዮጵያ  ከተፈጸሙ ወንጀሎች ጋር  ተያይዞ ሲንከባለሉ  የመጡ ጉዳዮችን በዘላቂነት በዕርቅ ለመቋጨት  የሚቋቋመውን የዕርቅ ኮሚሽን ምክር ቤቱ ከተወያየበት በኋላ ለሚመለከተው የፓርላማው አካል ለዝርዝር ዕይታ መምራቱ ተመልክቷል።   የአስተዳደር ወሰን እና ማንነትን በተመለከተ የሚነሱ ጥያቄዎችን እንዲሁም የሚቋቋመውን ኮሚሽን በተመለከትም ምክር ቤቱ ተወያይቶበታል።–ለዝርዝር ዕይታ እንደመራውም ...

Read More »

የአለም የፕሬስ ነጻነት ቀን በኢትዮጵያ እንዲከበር ተወሰነ

(ኢሳት ዲሲ–ሕዳር 20/2011) የ2019 የአለም የፕሬስ ነጻነት ቀን በኢትዮጵያ እንዲከበር መወሰኑን ዩኔስኮ በይፋ አስታወቀ። የመገናኛ ብዙሃን ሚኒ በዲሞክራሲና ምርጫ ላይ በሚል ርዕስ እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር ከግንቦት 2 እስከ 3 በአዲስ አበባ የሚካሄደውን 26ኛውን የፕሬስ ነጻነት ቀን ዩኔስኮ ከኢትዮጵያ መንግስትና ከአፍሪካ ህብረት ጋር በትብብር ማዘጋጀቱ ታውቋል። የተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣የሳይንስና የባህል ድርጅት ዩኔስኮ ትላንት በይፋ እንዳስታወቀው በአዲስ አበባ በአፍሪካ ሕብረት ጽሕፈት ቤት ...

Read More »