ኢትዮጵያ 20 ቢሊዮን የሚሆን ዶላር በሕገወጥ መንገድ እንደሸሸባት ታወቀ

(ኢሳት ዲሲ–የካቲት 6/2011)ኢትዮጵያ ባለፉት ዘጠኝ ዓመታት ውስጥ 20 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ ወደ ውጭ በሕገወጥ መንገድ እንደሸሸባት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን አስታወቀ። በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን  ይፋ ያደረገው የአፍሪካ የጤና ክብካቤና የኢኮኖሚ ዕድገት ሪፖርት እንዳመለከተው ይህ ገንዘብ ኢትዮጵያ ለጤናው ዘርፍ የምታውለውን 87 በመቶ በጀት ይሸፍናል። በአዲስ አበባ ይፋ የተደረገው የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ሪፖርት፣ ኢትዮጵያ ኣኝደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር ከ2003 እስከ ...

Read More »

የተፈናቀሉ 46 ሺህ የሚሆኑ ዜጎች መንግስት በቂ የሆነ እርዳታ እያደረገልን አይደለም አሉ

(ኢሳት ዲሲ–የካቲት 6/2011)ከማዕከላዊና ምዕራብ ጎንደር ዞኖች የተፈናቀሉ 46 ሺህ የሚሆኑ ተፈናቃዮች መንግስት በቂ የሆነ የምግብ እና ቁሳቁስ ድጋፍ እያቀረበላቸው አለመሆኑን ገለጹ። በሁለቱ ዞኖች በተከሰተው የፀጥታ ችግር ምክንያት ከቀያቸው የተፈናቀሉ ዜጎች መንግስት በቂ የሆነ የምግብ ፣የውሃ ፣የጤና እና ቁሳቁስ ድጋፍ እያቀረበላቸው አለመሆኑን ገልጸዋል ። በአካባቢው ያለው ሁኔታ አሁንም የተረጋጋ አለመሆኑ ይነገራል። ይሕ በእንዲህ እንዳለም በህገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወሩ የነበሩ 43 ክላሽሸንኮቭ ...

Read More »

በሕንድ በአንድ ሆቴል በተነሳ ቃጠሎ 17 ሰዎች ሞቱ

(ኢሳት ዲሲ–የካቲት 5/2011)በሕንድ ደልሂ በአንድ ሆቴል ውስጥ ዛሬ ማለዳ በተነሳ ቃጠሎ 17 ሰዎች ሞቱ። ቢቢሲ ከስፍራው እንደዘገበው በአብዛኛው ቱሪስቶች በሚበዙበትና ዋጋው ዝቅተኛ በሆነው አርፒት ፓላስ ሆቴል በተነሳው ቃጠሎ ሴቶችንና ህጻናትን ጨምሮ የ17 ሰዎች ህይወት አልፏል። ከሟቾቹ ከፊሉ እሳቱን ለመሸሽ በመስኮት ሲዘሉ መሞታቸው የተገለጸ ሲሆን ብዙዎቹ የሞቱት ግን ታፍነው መሆኑን የአካባቢው መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል። የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች የ35 ሰዎችን ህይወት የታደጉ ...

Read More »

የብሔራዊ ዕርቀ ሰላም ኮሚሽን ከዘር፣ ከሃይማኖት እና ከመድሎ በጸዳ መልኩ እንዲሰራ ተጠየቀ

(ኢሳት ዲሲ–የካቲት 5/2011)በቅርቡ በኢትዮጵያ የተቋቋመው የብሔራዊ ዕርቀ ሰላም ኮሚሽን ከዘር፣ ከሃይማኖት እና ከመድሎ በጸዳ መልኩ ስራቸውን በአግባቡ እንደሚወጡ ዕምነታቸው መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ገለጹ። የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ካርዲናል አቡነ ብርሃነ ኢየሱስ የኮሚሽኑ ሰብሳቢ ሆነው ተመርጠዋል። በጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽሕፈት ቤት ከብሔራዊ ዕርቀ ሰላም ኮሚሽን አባላት ጋር የተነጋገሩት ዶክተር አብይ አህመድ ይህ በመቶ ዓመት አንዴ የሚገኝ አጋጣሚ ሃገርን ከማቀራረብና ሰላምን ከማምጣት ...

Read More »

በምዕራብና ማዕከላዊ ጎንደር የተፈናቀሉ ዜጎች ቁጥር 46ሺህ ደረሰ

(ኢሳት ዲሲ–የካቲት 5/2011)በምዕራብና ማዕከላዊ ጎንደር በተፈጠረው ግጭት የተፈናቀሉ ዜጎች ቁጥር 46ሺህ መድረሱ ተገለጸ። በህወሃት አገዛዝ ቀጥተኛ የመሳሪያና የገንዘብ ድጋፍ የሚካሄድ ነው በተባለው በዚሁ ግጭት በ12 ቀበሌዎች የሚገኙ ቤቶች በእሳት መውደማቸውንም የደረሰን መረጃ ያመለክታል። ከቅማንትና ከአማራው ማህብረሰብ የተፈናቀሉት እነዚህ ዜጎች በምግብና ውሃ እጥረት ስቃይ ላይ መሆናቸው ተገልጿል። ተፈናቃዮቹ በአርማጮሆና ደምቢያ አካባቢዎች ተጠልለው ይገኛሉ። አስቸኳይ እርዳታ እንዲቀርብላቸው የጠየቁት ተፈናቃዮች አለበለዚያ በበሽታና በረሃብ ...

Read More »

የናይጄሪያ የምርጫ ኮሚሽን በእሳት ጋየ

(ኢሳት ዲሲ–የካቲት 4/2011)የናይጄሪያ የምርጫ ኮሚሽን በእሳት መጋየቱ ተሰማ። የምርጫ ኮሚሽኑ ቃጠሎ በሃገሪቱ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ሊካሄድ አንድ ሳምንት ብቻ በቀረበት በዚህ ሰአት መፈጸሙ አነጋጋሪ ሆኗል። በናይጄሪያ ፕላቶ በተባለው ግዛት የሚገኘው የምርጫ ኮሚሽኑ ጽህፈት ቤት በተነሳው ቃጠሎ ለምርጫው የሚያስፈልጉ ቁሶችና የድምጽ መስጫ ሳጥኖች ጭምር መውደማቸው ታውቋል። ከ36ቱ የናይጄሪያ ግዛቶች አንዱ በሆነውና በሃገሪቱ ማዕከላዊ ክፍል ውስጥ በሚገኘው ፕላቶ ግዛት በምርጫ ኮሚሽኑ ጽህፈት ቤት ...

Read More »

የግብፁ ፕሬዝዳንት የወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር ሆኑ

(ኢሳት ዲሲ–የካቲት 4/2011)የግብፁ ፕሬዚዳንት አል ሲሲ የወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር ሆነው ተመረጡ፡፡ ላለፉት ሁለት አመታት የአፍሪካ ህብረትን በሊቀመንበርነት ሲመሩ የነበሩት ፕሬዝዳንት ፓል ካጋሜ ሊቀመንበርነታቸውን አስረክበዋል፡፡ አል ሲሲ የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር በመሆን እስከ ፈረንጆቹ 2020 ይቆያሉ ተብሏል፡፡ ፓል ካጋሜ ባደረጉት ንግግር ለአፍሪካ ሀገራት መንግስታት፣ ተቋማት እና ሌሎች አካላት በቆይታቸው ሲያደርጉላቸው ለነበረው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል፡፡ አል ሲሲ በበኩላቸው በአፍሪካ የድርድር እና የመከላከል ...

Read More »

ሌተናል ኮለኔል ትርሲት ገብረመስቀል አረፉ

(ኢሳት ዲሲ–የካቲት 4/2011)የቀድሞው የኢትዮጵያ አየር ሃይል ባልደረባና የሶማሊያ ጋር በተደረገው ጦርነት ተሳታፊ የነበሩት ሌተናል ኮለኔል ትርሲት ገብረመስቀል ከዚህ አለም በሞት ተለዩ። በሌላም በኩል በአሜሪካ ሂዩስተን ከተማ ከኢሳት አስተባባሪዎች አንዱ የነበሩት አቶ አብይ ግርማ ከዚህ አለም በሞት ተለይተዋል። ለእረፍት ወደ አሜሪካ ብቅ ባሉበት በድንገት ከዚህ አለም በሞት የተለዩት ሌተናል ኮለኔል ትርሲት ገብረመስቀል በምርጫ 1997 ቅንጅት ለአንድነትና ለዲሞክራሲ ፓርቲን በመወከል የአዲስ አበባ ...

Read More »

በደቡብ ጎንደር አንድ መስጊድ በእሳት ተቃጠለ

(ኢሳት ዲሲ–የካቲት 4/2011)በደቡብ ጎንደር ትላንት ምሽት በአንድ መስጊድ ላይ የእሳት ቃጠሎ መድረሱ ተሰማ። የእሳት አደጋው የደረሰው በደቡብ ጎንደር ዞን አንዳቤት ወረዳ ጃራ ገዶ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ መሆኑንም የኢሳት ምንጮች ገልጸዋል። የዘር ግጭትን ወደ ሃይማኖት ግጭት ለመቀየር የሚጥሩ ወገኖች ይሄን ችግር እንደፈጠሩትም ምንጮቹ ጨምረው ገልጸዋል። በቅርቡ በዚሁ በደቡብ ጎንደር ዞን እስቴ ከተማ ሁለት መስጊዶች መቃጠላቸውና በሶስተኛው መስጊድ ላይ ከባድ ጉዳት መድረሱና ...

Read More »

ሴራሊዮን አስገድዶ መድፈር ላይ የድንገተኛ ጊዜ መመሪያ አወጣች

(ኢሳት ዲሲ–የካቲት 1/2011)ሴራሊዮን በሐገሯ በሴቶች ላይ የሚፈጽመው አስገድዶ መድፈር አሳሳቢ ሆኖ በመገኘቱ የድንገተኛ ጊዜ መመሪያ ማውጣቷን አስታወቀች። ሴት በመድፈር የተጠረጠረና የተፈረደበት ሰው በእድሜ ልክ እስራት እንደሚቀጣም የሃገሪቱ ፕሬዝዳንት አስታውቀዋል። በሴራሊዮን በሴቶች ላይ የሚፈጸመው አስገድዶ የመድፈር ወንጀል እየጨመረና አሳሳቢ ሆኖ መገኘቱን በመግለጽ የድንገተኛ ጊዜ መመሪያ መውጣቱን ትላንት በርዕሰ መዲናዋ ፍሪታውን ያስታወቁት የሐገሪቱ ፕሬዝዳንት ጁሊየስ ማዳባዩ መንግስት አደጋውን ለመቀነስ ቁርጠኛ መሆኑን አስታውቀዋል። ...

Read More »