ለጌዲዮ ተፈናቃዮች አስቸኳይ እርዳታዎች ካልደረሱ አደጋው ከዚህ የከፋ እንደሚሆን ተገለጸ

(ኢሳት ዲሲ–መጋቢት 6/2011)ለጌዲዮ ተፈናቃዮች የሚያስፈልጉ አስቸኳይ ርዳታዎች ካልደረሱላቸው የሚደርሰው አደጋ የከፋ እንደሚሆን በአካባቢው የተሰማሩ የህክምና ባለሙያዎች ገለጹ። ተፈናቃዮቹ አሁን ካሉበት አስከፊ ሁኔታ ጋር ተያይዞ ሌሎች ተላላፊ የሆኑ በሽታዎች የመከሰት እድላቸው ሰፊ መሆኑንም ገልጸዋል ከህክምና ቡድኑ አባላት አንዱ ከኢሳት ጋር በነበራቸው ቆይታ። የጤና ጥበቃን ጨምሮ የመንግስት አካላት፣መላው ኢትዮጵያውያን፣መንግስታዊ ያልሆኑ የእርዳታ ድርጅቶችና ጉዳዩ ይመለከተናል የሚሉ አካላት ሁሉ አደጋ ላይ ላሉት ለነዚህ ወገኖች ...

Read More »

የአማራ ክልል ተፈናቃዮችን ለማቋቋም ቴሌቶን ሊካሄድ ነው

(ኢሳት ዲሲ–መጋቢት 6/2011)በአማራ ክልል እና ከክልሉ ወጭ የተፈናቀሉ ከ1 መቶ ሺህ በላይ አማራዎችን ለማቋቋም ታዋቂ ባለሀብቶች የሚሳተፉበት ቴሌቶን በነገው እለት በሼራተን ሆቴል እንደሚካሄድ ተነገረ። በአማራ ክልል እና ከክልሉ ውጭ የተፈናቀሉ ዜጎችን መልሶ ለማቋቋም 1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ያስፈልጋል ተብሏል፡፡ በሸራተን አዲስ ሆቴል ነገ በሚካሄደው የድጋፍ ማሰባሰቢያ ቴሌቶን ታዋቂ ባለሀብቶችና ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ይገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡ የገቢ ማሰባሰቢያ ቴሌቶኑ 90 ...

Read More »

በሱልልታ ከተማ ነዋሪዎች በስጋት እና በሰቆቃ እየኖሩ መሆናቸውን ገለጹ

(ኢሳት ዲሲ–መጋቢት 6/2011) በኦሮሚያ ክልል አዲስ አበባ አቅራቢያ የምትገኘው ሱልልታ ከተማ በ7 ቀናት ውስጥ ቤታችሁ ይፈርሳል የተባሉ ነዋሪዎች በስጋት እና በሰቆቃ እየኖሩ መሆናቸውን ገለጹ። የሱልልታ እና የአካባቢው  ነዋሪዎች  የኦሮሚያ ክልል መንግስት ቤታችን ሊያፈርስ ቀይ ምልክት አስምረውብናል፥ ከመፈናቀላችን በፊትም ድረሱልን ሲሉ ጥሪ አሰምተዋል ፡፡ የጎረቤቶቻችን እና የአንዳንዶችን ቤት ግን ለይተው ትተውታል ሲሉም ምሬታቸውን ገልጸዋል፡፡ በሱልልታ ከተማ አስተዳደር ለቤቶቹ መፍረስ የተሰጠው ምክንያት ...

Read More »

የሃዋሳ ከተማ ነዋሪዎች ስጋት ላይ መውደቃቸውን ገለጹ

(ኢሳት ዲሲ–መጋቢት 5/2011) በሀዋሳና አካባቢዋ ኤጄቶ በሚል የሚጠራው ቡድን ከጠራው አድማ ጋር ተያይዞ በከተማዋ ምንም አይነት እንቅስቃሴ ባለመኖሩ የከተማዋ ነዋሪው ስጋት ላይ መውደቁን ነዋሪዎች ገለጹ። የሚያቀርቡት ጥያቄ ትክክል ቢሆንም እየሄዱበት ያለው አካሄድ ግን ትክክለኛ ያልሆነና የሌላውን መብት የሚገፍ ነው ብለዋል። የሲዳማ አርነት ንቅናቄ በበኩሉ ኤጄቶ የጠራው አድማ ተጠንቶና ታስቦበት የተደረገ ነው፣እኛም ይህን አድማ እንደግፈዋለን ብሏል። ይሄ እንዲሆን ያደረጉት ደግሞ የሲዳማ ...

Read More »

የጌዲዮ ተወላጆች በመሆናቸው ብቻ ከመንግስት ስራ መባረራቸውን ገለጹ

(ኢሳት ዲሲ–መጋቢት 5/2011)በምዕራብ ጉጂ ዞን ቃርጫ ወረዳ ከመንግስት ስራ የተባረሩ  የጌዲዮ ተወላጆች የከፋ ችግር ውስጥ መውደቃቸውን ለኢሳት ገለጹ። ተወላጆቹ እንደሚሉት ከስራ እንዲባረሩ የተደረገው የጌዲዮ ተወላጆች በመሆናቸውና ማንነታችን ይገለጽ፣በቋንቋችን እንማር የሚል ጥያቄ በማቅረባቸው ነው። ከስራ ሲባረሩ ያለምንም ክፍያ መሆኑ ደግሞ የነሱንም ሆነ የቤተሰባቸውን ኑሮ አስከፊ እንዲሆን እንዳደረገባቸው ይናገራሉ። በምዕራብ ጉጂ ዞን ቃርጫ ወረዳ ከሚያዚያ 2010 በፊት የመንግስት ሰራተኛ ነበሩ። ነገር ግን ...

Read More »

አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ሙሉ በሙሉ የፖለቲካ ምህዳሩ መዘጋቱን ገለጹ

(ኢሳት ዲሲ–መጋቢት 5/2011)በኢትዮጵያ በየክልሉ ያሉ የኢህአዲግ መዋቅር አባላት ከቀደመው ስርዓት በከፋ መልኩ ሙሉ በሙሉ የፖለቲካ ምህዳሩን እንደዘጉት የአርበኞች ግንቦት ሰባት ዋና ጸሃፊ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ገለጹ። አቶ አንዳርጋቸው ከጀርመን ድምጽ ራዲዮ ጋር ባካሄዱት ቃለ ምልልስ ዶክተር አብይ ስልጣን እንደያዙ የፖለቲካ ምህዳሩ መስፋት ቢጀምርም የኢህአዴግ መዋቅር የዜግነት ፖለቲካ አራማጅ ድርጅቶችን በጠላትነት ፈርጀው እንቅስቃሴያቸውን ገድበዋል ብለዋል። አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ እንዳሉት ዘርን እና ...

Read More »

አርበኞች ግንቦት ሰባት ለአንድነትና ለዲሞክራሲ ለአጥፊ ጽንፈኞች አገራችንን እንዳናስረክብ ልንጠነቀቅ ይገባል ሲል አሳሰበ

 (ኢሳት ዲሲ–መጋቢት 4/2011) ለዘላቂው የሚበጀንን ለዘብተኛውን መንገድ ትተን ዋልታ ለረገጡ አጥፊ ጽንፈኞች አገራችንን እንዳናስረክብ ልንጠነቀቅ ይገባል ሲል አርበኞች ግንቦት ሰባት ለአንድነትና ለዲሞክራሲ ንቅናቄ አሳሰበ። ንቅናቄው በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ባወጣው መግለጫ እንዳለው  በኢትዮጵያ የታየው የለውጥ ሂደት የፈጠረው ተስፋ  ቀስ በቀስ ጥግ በያዙ አክራሪዎችና  የቡድንን ፍላጎት ብቻ ባስቀደሙ ኃይሎች ግፊትና ጫጫታ ሊሰናከል ወደሚችል አደገኛ አቅጣጫ እየተገፋ ይገኛል። እናም ሀገር የባሰ አደጋ ላይ ...

Read More »

ፍርድ ቤቱ በእነ አቶ በረከት ላይ ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ፈቀደ

 (ኢሳት ዲሲ–መጋቢት 12/2011)የባህርዳርና አካባቢዋ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በአቶ በረከት ስምዖንና አቶ ታደሰ ካሳ ላይ የ8 ቀናት ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ፈቀደ። ፍርድ ቤቱ የክልሉ ፀረ ሙስና ኮሚሽን መርማሪ በአቶ በረከት ስምኦንና አቶ ታደሰ ካሳ ላይ ከጠየቀው ይ14 ቀናት ጊዜ ውስጥ የ8 ቀን ተጨማሪ ብቻ የምርመራ ጊዜ ፈቅዷል። የባህርዳርና አካባቢዋ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በትናንትናው ዕለት በጥረት ኮርፖሬት ዝርፊያ ፈጽመዋል ተብለው የተጠረጠሩትን አቶ ...

Read More »

የድሬዳዋ ከተማ ከንቲባ ከኃላፊነታቸው ለቀቁ

(ኢሳት ዲሲ–መጋቢት 3/2011)የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ኢብራሂም ዑስማን ከኃላፊነታቸው ለቀቁ። አቶ ኢብራሂም ዑስማን ስልጣናቸውን ለመልቀቅ ለከተማ አስተዳደሩ ያቀረቡት ጥያቄ በምክር ቤቱ ተቀባይነት አገኝቷል፡፡ በምትካቸውም ምክርቤቱ አቶ መሐዲ ዲሬን የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ በማድረግ ሹሟል፡፡ የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ በነበሩት አቶ ኢብራሂም ዑስማን  ላይ በተደጋጋሚ በሚደረጉ ሠልፎች ተቃውሞ ይቀርብባቸው ነበር፡፡ ድሬድዋ ከተማዋን በፈረቃ በሚያስተዳድሩ ፓርቲዎች ስትታመስ መቆይቷም ነው የሚታወቀው። አንዴ ሶህዴፓ ...

Read More »

በኢትዮጵያ አማካይ አገራዊ የዋጋ ግሽበት በ13 በመቶ ጭማሪ ማሳየቱ ተገለጸ

 (ኢሳት ዲሲ–መጋቢት 12/2011)በኢትዮጵያ የካቲት ወር ላይ የተመዘገበው አማካይ አገራዊ የዋጋ ግሽበት በ13 በመቶ ጭማሪ ማሳየቱን የማዕከላዊ ስታቲስቲክስ ኤጀንሲ አስታወቀ፡፡ ኤጀንሲው ባወጣው መግለጫ ይፋ እንዳደረገው፣ ረዘም ያለ ጊዜ የዋጋ ግሽበት ሁኔታን  በሚያሳይ የ12 ወራት ተንከባላይ አማካይ የዋጋ ግሽበትኝ በተመለከተ በተደረገው ምዘና፣ በዚህ ዓመት የካቲት ወር  አገራዊ የምግብ የዋጋ ግሽበት በ11.7 በመቶ ዕድገት አሳይቷል፡፡ የ12 ወራት ተንከባላይ አማካይ አገራዊ ምግብ ነክ ያልሆኑ ...

Read More »