በአዲስ አበባ ባላደራው ምክር ቤት (ባልደራስ) አባላት ላይ የሚደርሰው እንግልትና እስር ቀጥሏል

(ኢሳት ዲሲ–ግንቦት 16/2011)በአዲስ አበባ ባላደራው ምክር ቤት (ባልደራስ) አባላት ላይ እየደረሰ ያለው እንግልትና እስር መቀጠሉ ተገለጸ። የምክር ቤቱ አባል አቶ ሽመልስ ለገሰ ዛሬ ከመኖሪያቸው የተፈናቀሉ ዜጎችን ጉዳይ ሊከታተሉ በሄዱበት በፖሊስ መታሰራቸው ተሰምቷል። ከሰአታት ክርክር በኋላም አቃቤ ህግ ስህተት አላገኘሁባቸውም ስለዚህ ክስ አልመሰርትም በማለቱ መለቀቃቸው ነው የታወቀው። በአዲስ አበባ አራት ኪሎ አካባቢ ቤታቸው ፈርሶ ቤት ሳያገኙ በላስቲክ ያሉ ዜጎችን ጉዳይ ሊያዩ ...

Read More »

በቤንሻንጉል ሁለት የመንግስት ሃላፊዎች ታሰሩ

(ኢሳት ዲሲ–ግንቦት 16/2011)በቅርቡ በቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል መተከል ዞን ከተፈጠሩ የጸጥታ ችግሮች ጋር በተያያዘ ሁለት የመንግስት ሃላፊዎች መታሰራቸው ተገለጸ። የቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል በወቅቱ ሁኔታ ላይ መክሮ የተለያዩ ውሳኔዎችን ማሳለፉን የደረሰን መረጃ አመልክቷል። በቁጥጥር ስር የዋሉት የመተከል ዞን አስተዳደርና ፀጥታ ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ አቶ ፋንቻ አምሳያ እና የግልገል በለስ ከተማ ከንቲባ አቶ ጊሳ ዚፋህ መሆናቸው ታውቋል። የቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል ባስተላለፈው አስቸኳይ ውሳኔ ...

Read More »

በኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ላይ የደረሰው አደጋ እንዳይከሰት ማድረግ ይቻል እንደነበር ተገለጸ

(ኢሳት ዲሲ–ግንቦት 15/2011)በኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ላይ የደረሰው አደጋ እንዳይከሰት ማድረግ ይቻል ነበር ሲል የአሜሪካን አውሮፕላን አብራሪዎች ማህበር አስታወቀ። የማህበሩ ቃል አቀባይን ጠቅሶ ሲ ኤን ኤን እንደዘገበው ባለፈው ህዳር ወር የአሜሪካን አውሮፕላን አብራሪዎች አባላት ለቦይንግ ኩባንያ ችግሩን አስረድተው ጥንቃቄ እንዲደረግ ያቀረቡት ሀሳብ ተቀባይነት ቢያገኝ ኖሮ አደጋ ሊከሰት አይችልም ነበር ብለዋል። የቦይንግ ኩባንያ የአደጋውን መንስዔ በተመለከተ በተለያዩ ጊዜያት የሚያቀርባቸውን ምክንያቶች የአብራሪዎቹ ...

Read More »

ለጌዲዮ ተፈናቃዮች ኢትዮጵያውያን አፋጣኝ ድጋፍ እንዲያደርጉ ተጠየቀ

(ኢሳት ዲሲ–ግንቦት 15/2011)በጌዲዮ ተፈናቃዮች ላይ የደረሰው ጉዳት ከፍተኛ በመሆኑ ኢትዮጵያውያን አፋጣኝ ድጋፍ እንዲያደርጉላቸው ዓለም ዓቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያውያን መብት ግሎባል አሊያንስ ጥሪ አደረገ። የድርጅቱ አመራሮች ሰሞኑን በጌዲዮ ጉብኝት አድርገው ከተመለሱ በኋላ ለኢሳት እንደገለጹት ተፈናቃዮቹ ከደረሰባቸው አካላዊ ጉዳት የበለጠ የስነልቦናው ጥቃት አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል። የግሎባል አሊያንስ ዳይሬክተር አርቲስትና አክቲቪስት ታማኝ በየነ ችግሩ ጥልቅ ነው ኢትዮጵያውያን ከምን ጊዜውም በላይ ተረባርበው ለወገናቸው መድረስ ...

Read More »

በድሬዳዋ ሳተናው የተሰኘው ማህበር አመራሮችና አባላት ላይ እስራትና እንግልት እየተፈጸመባቸው ነው

(ኢሳት ዲሲ–ግንቦት 15/2011)በድሬዳዋ ያለውን ኢፍትሃዊነት ለመታገል በከተማዋ ወጣቶች የተቋቋመው ሳተናው የተሰኘው ማህበር አመራሮችና አባላት ላይ እስራትና እንግልት እየተፈጸመ መሆኑ ተገለጸ። የማህበሩ ሊቀመንበር በፖሊስ ተይዞ ከታሰረ ወዲህ ቤተሰቦቹ እንዳይጠይቁት መደረጉን ነዋሪዎች ለኢሳት ገልጸዋል። 40 40 20 የተሰኘው የከተማዋ አስተዳደራዊ መዋቅር የድሬዳዋን ነዋሪዎች ባይተዋር ያደረገ ነው፡፡ መብታቸውን የገፈፈ ጨቋኝ መዋቅር ነው የሚል ተቃውሞ ይዞ የተነሳው የሳተናውን ማህበር ለማጥፋት የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር አፈና ...

Read More »

በአዲስ አበባ የተካሄዱት ህገወጥ ግንባታዎች በባለሀብቶችና የፖለቲካ ፓርቲዎች የተካሄደ መሆኑ ተገለጸ

(ኢሳት ዲሲ–ግንቦት 15/2011)በአዲስ አበባ በ5 ክፍለከተሞች ባለፉት ሁለት ሳምንታት የተካሄዱት ህገወጥ ግንባታዎች በባለሀብቶችና የፖለቲካ ፓርቲዎች አማካኝነት መሆኑን የአዲስ አበባ አስተዳደር የከንቲባ ጽሕፈት ቤት አስታወቀ። ምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ከመሬት ወረራውና ህገወጥ ግንባታው ጋር በተያያዘ ሁለት የፖለቲካ ፓርቲዎች እጃቸው እንዳለበት ገልጸዋል። በስም እነማን እንደሆኑ ግን አልጠቀሱም። የከንቲባው ጽሕፈት ቤት የፕሬስ ክፍል ሃላፊ ወይዘሪት ፌቨን ተሾመ ለኢሳት ...

Read More »

ቻይና ለቦይንግ ኩባንያ የካሳ ጥያቄ አቀረበ

(ኢሳት ዲሲ–ግንቦት 14/2011) ቻይና ለቦይንግ ኩባንያ የካሳ ጥያቄ ማቅረቧ ተሰማ። በኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ላይ የደረሰውን አደጋ ተከትሎ የቦይንግ ምርት የሆኑ ማክስ 737 አውሮፕላኖችን በሙሉ ከበረራ ውጪ እንዲሆኑ ያደረገችው ቻይና በዚህም ምክንያት የደረሰብኝን ኪሳራ ቦይንግ ኩባንያ ይክፈለኝ ስትል መጠየቋ ተሰምቷል። ከቻይና ሌላ የቱርክና የዱባይ አየር መንገዶችም የካሳ ክፍያ መጠየቃቸውን ሮይተርስ ዘግቧል። በተያያዘ ዜና ባለቤታቸው በኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን አደጋ ህይወታቸውን ...

Read More »

በሶማሊያ የጦር ወንጀል ፈጽሟል የተባለው ግለሰብ ለእስር ተዳረገ

(ኢሳት ዲሲ–ግንቦት 14/2011)በአሜሪካን ኡበር የተሰኘ የታክሲ አገልግሎት ሹፌር በሶማሊያ የጦር ወንጀል በመፈጸሙ ለእስር ተዳረገ። የቀድሞ የሶማሊያ መሪ የዚያድ ባሬ ወታደራዊ ኮማንደር ከ30ዓመታት በፊት ከፍተኛ የሰብዓዊ መብት ጥሰት በመፈጸም በጦር ወንጀለኝነት የሚፈለግ እንደነበር ቢቢሲ ዘግቧል። ትላንት በቨርጂኒያ አሌክሳንደሪያ የተሰየመው ችሎት ኮሎኔል ዩሱፍ ዓሊን ጥፋተኛ ብሎ ውሳኔ ሰጥቷል። ኡበር የታክሲ አገልግሎትም ኮሎኔሉን ማባረሩን አስታውቋል። በዚያድ ባሬ አገዛዝ ኮሎኔል የነበሩትና በአሜሪካን የኡበር ሹፌር ...

Read More »

የኢቢሲ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ስራ ለቀቁ

(ኢሳት ዲሲ–ግንቦት 14/2011)የኢትዮጵያ ብሮድካስት ኮርፖሬሽን /ኢቢሲ / ዋና ሥራ አስፈጻሚ  አቶ ስዩም መኮንን ከኃላፊነታቸው መልቀቃቸውን ለድርጅቱ ሰራተኞች አሳወቁ ። ዶክተር ንጉሴ ምትኩ ሊተኳዋቸው እንደሚችሉ የኢሳት ምንጮች ተናገሩ   ። ከ2008 ዓም ጀምሮ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሸን (ኢቢሲ) ዋና ሥራ አስፈጻሚ በመሆን ሲያገለግሉ የቆዩት አቶ ሥዩም መኮንን በትላንትናው እለት  ግንቦት 13 ቀን 2011 ዓ.ም. ከኃላፊነታቸው መልቀቃቸውን ለድርጀቱ ሠራተኞች አስታወቁ፡፡ አቶ ሥዩም የኮርፖሬሸኑን የዘጠኝ ...

Read More »

በአስተዳደራዊ ችግር እና በሙስና በየፍርድ ቤቱ የሚንገላቱ ካህናትን ታደጓቸው በሚል ጥሪ ቀረበ

(ኢሳት ዲሲ–ግንቦት 14/2011)በአስተዳደራዊ ችግር እና በሙስና በየፍርድ ቤቱ የሚንገላቱ ካህናትን ታደጓቸው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ለቅዱስ ሲኖዶስ አባቶች ጥሪ አደረጉ። ዛሬ በተጀመረው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቅዱስ ሲኖዶስ የርክበ ካህናት መደበኛ ስብሰባ ላይ የተገኙት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ቅዱስ ሲኖዶሱ ቤተክህነቱን እንዲያጠናክርም ጠይቀዋል። ቅዱስ ሲኖዶሱ በዘረኝነት እንዳይጠቃ ካህናት ትልቅ ሃላፊነት እንዳለባቸውም ጠቅላይ ሚኒስትሩ አሳስበዋል። በመጪው ክረምት 4 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል ...

Read More »